fredag 15. mai 2015

አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን። የጋራ መግለጫ

stamps Joint press release
አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን።
የአንድነት፣ የመከባበር፣ የመቻቻል እና የነፃነት ምሳሌ የሆነችው አገራችን እኩይ አላማቸውን ለማሳካትና የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም በሚንከላወሱት የወያኔ ቡደን አገራችንና ሕዝባችን ከምንግዜውም በከፋ ደረጃ ላይ አድርሰዋታል።
ወጣቱ በአገሩ ላይ ተምሮና ሰርቶ የመኖር እድሉ ለወያኔው አገዛዝ ማደር አልያም አገሩን ጥሎ መሰደደ በሆነበት ሁኔታ ውስጥ አገሩን ጥሎ የሚሰደደው ዜጋ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለመሰደድ በሚያደርገው ጉዞ ምን ያህሉ በበርሃ እንደሚቀርና የአሳ እራት እንደሆነ የመገናኛ ብዙሃን በሰፊው ሲዘግቡት ቆይተዋል።
በተለያየ አገር በስደት ከሚፈልጉት አገር የደረሱትና የእለት ጉርሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለማገዝ ደፋ ቀና በሚሉበት ሂደት ውስጥ በደቡብ አፍሪካ በቁማቸው በአሳት መቃጠል፣ በሊቢያ አይናቸው እያየ መታረድና በጥይት መደብደብ ሆኗል እጣ ፋንታቸው።
እናም አገርና ሕዝብ በእንደዚህ አይነት አስከፊ ሂደት መቀጠል የለበትም የወያኔም የግፍ አገዛዝ ሊበቀው ይገባል በሚል ቀደም ብለን ይህን በታኝ ስርዓት በትጥቅ ትግል እየተፋለምን ያለን ደርጅቶች እኛ አንድ ሆነን ሕዝቡን አንድ በማደረግ አገራቸንና ሕዝባችንን ነፃ ማውጣት የሚገባን ወቅት አሁን ነው በሚል ስርዓቱን ለማስወገድ በሚደረገው የትግል ሂደት በትብብር መስራት አለብን በሚል ውይይት ጀምረናል።
ወደፊት በሚኖረው የትግል ሂደት በትብብር፣ በጥምረት ብሎም በውህደት ለመስራት በውይይት ላይ የምንገኘው ድርጅቶች፡-
1. የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
2. የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
3. የቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
4. የአማራ ዴሞክራሲ ሃይል ንቅናቄ
5. አረበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ
ስንሆን ከሁሉም አስቀድመን አገራችንና ሕዝባችን ማዳን ግባችን አድርገን እንስራ በሚል መርህ በማንኛውም መንገድ አብረን መስራት አለብን ወደ ፊት ምንም አይነት ልዩነት ይኖረናል ብለን ባናምንም በሂደት ወደ አንድ የምንመጣበትን ሁኔታ እያመቻቸን አሁን ግን አገርና ሕዝብን የማዳኑን ስራ እንጀምር በሚል ውይይት እያደረግን መሆናችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መግለፅ እንወዳለን።
አምባገነኑም የወያኔ ቡድን እንዳለፉት ምርጫዎች ሁሉ በቅርቡ የሚደረገውን የይስሙላ ምርጫ ለማድረግ ደፋ ቀና እያለ ሲሆን በተለያየ አገራት በእናትህ፣ በአባትህ፣ በወንድምህ፣ በእህትህ ላይ ላይ እየደረሰ ላለው ዘግናኝ ግፍ እንኳን ወቅቱን ጠብቆ ተቃውሞውን ያልገለፀ ኢትዮጵያዊ ባህሪ የለሌው እኩይ ሥርዓት በመቃወም ረገድ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገህ ቢሆንም በተደራጀ ሁኔታ እየታገልን ከምንገኘው ተቃዋሚ ድርጅቶች ጎን በመሰለለፍ አስፈላጊውን አስተዋጽዖ እንድታደርግ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
አንድነት ሃይል ነው!!!
30/08/2007 ዓ.ም

አይሲስን ስንቃወም ህወሓትን አለመርሳት!

May 13, 2015
በአይሲስ በግፍ በታረዱብን ወገኖቻችን የተሰማን ሀዘንና ቁጭት ከፍተኛ ቢሆንም እንኳን ከአዕምሮዓችን መውጣት የሌለበት ሀቅ አለ። ይህ ሀቅ “ያስጠቃን፣ ያሳረደን ወያኔ ነው” ከሚለውም ያለፈ ነው። መረሳት የሌለበት ሀቅ፣ ከአይሲስ የከፋ ጨካኝ በአገራችን የመንግሥት ሥልጣን የተቆጣጠረ መሆኑ ነው።
የህወሓት ፋሽስት ጦር በበደኖ፣ በአዋሳ፣ በሀረር፣ በጋምቤላ፣ በጎንደር፣ በኦጋዴን፣ በአዲስ አበባ፣ በሸካና መዠንገር፤ እንዲሁም በሚታወቁም በማይታወቁም የማሰቃያ እስር ቤቶች አይሲስ እየፈፀመ ካለው የባሱ ወንጀሎች በወገኖቻችን ላይ ፈጽሟል፤ አሁንም እየፈፀመ ነው። ባሳለፍነው ሣምንት እንኳን በሁመራ ወገኖቻችን የራሳቸውን መቀበሪያ ጉድጓድ ቆፍረው በጅምላ ተገድለዋል። በአይሲስና በህወሓት መካከል ያለው ልዩነት አይሲስ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሩን በቪዲዮ እየቀረፀ ለዓለም ሲበትን ህወሓት ግን እነዚሁኑ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሮችን እየፈፀመ መረጃዎች አፍኖ መያዙ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ግን ህወሓት ሰዎችን ከነሕይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ የቀበረ አረመኔ፣ እኩይ ድርጅት ነው።
ስለሆነም ለዓለም ሰላም ስጋት የሆነውን አይሲስን ስንቃወም የራሳችንን አይሲስ – ህወሓትን – አለመርሳት እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት፣ የአይሲስን እኩይ ተግባራት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር እና ከዲሞክራሲያዊያዊ ፓለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ጋር ለማገናኘት እያደረገ ያለው ጥረት ምን ያህል አደገኛ ተግባር እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል። ዓይን አውጣ ሌባ ንፁሁን ሰው “ሌባ” እንደሚለው ሁሉ የኛው አይሲስ ራሱን ንፁህ አስመስሎ ሌሎችን “አይሲስ” ማለቱ ሊነቃበት ይገባል።
ሌላው ተያያዥ ጉዳይ ደግሞ ስለስደተኝነት የሚሰጠው ገለፃ ነው። ህወሓት ለስደተኝነት ምክንያቱ ደላሎች እንደሆኑ ይናገራል። ይህ የጉዳዩን ግንድ ትቶ ቅርንጫፎች ላይ ማትኮር ነው። ህገወጥ ደላሎች ራሳቸው ሊኖሩ የቻሉት ገንዘብ ከፍለውና የሕይወት ሪስክ ወስደው ለመሰደድ የሚፈልጉ ዜጎች በመኖራቸው ነው። ችግሩን በቅንነት ለመመርመር የሚፈልግ “ይህን ያህል ሰው የሕይወት ሪስክ እየወሰደ ከአገር ለመሰደድ ምን አነሳሳው?” ብሎ መጠየቅ እና ምላሽ ማግኘት ይኖርበታል። በሀገር ውስጥ በነፃነት ተረጋግቶ መኖር፣ ሠርቶ የማደግ ተስፋ ቢኖር ኖሮ ይኸን ያህል ሰው የአደጋውን ከፍተኛነት እያየ ለመሰደድ ይነሳሳ ነበርን? ኢትዮጵያዊው ከስደት ሊያገኝ የሚሻው ምንድነው? እንደ ወያኔ ካድሬዎች ገለፃ ከሆነ ከስደት ሊያገኝ የሚችለው አገሩ ውስጥ እያለለት ነው ኢትዮጵያዊ የሚሰደደው። ይህ ምን ዓይነት አመክኖ ነው? ከዚህ የባሰው ደግሞ ስደትንም የእድገት ውጤት አድርጎ የማቅረብ በሽታ ነው። ይህ እውነት ከሆነ፤ ህወሓት ለኢትዮጵያ አመጣሁላት የሚለው እድገት ውጤት ረሀብ፣ ስደት፣ መርዶ፣ እስር፣ ስቃይ፣ ሞት ከሆነ እንዴት “እድገት” ብለን እንጠራዋለን። ለስደተኝነት መብዛት ህገወጥ ደላሎችን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ፤ “እኔ ከደሙ ንፁህ ነኝ” የማለት ያህል ነው። በህጋዊዎቹም በህገወጦቹም ደላሎች ውስጥ የወያኔ ሰዎች በቀጥታም በተዘዋዋሪም እንዳሉበት መረጃዎች ያመለክታሉ። ገንዘብ ባላበት ሁሉ የወያኔ እጅ መኖሩ ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። የሰዎች ዝውውር የህወሓት አንዱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ መሆኑ የማይታበል፤ በቀላሉ ማረጋገጥ የሚቻል ሀቅ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በዓለም አቀፉ አይሲስ አረመኔያዊ ተግባሮች በደረሰብን የመጠቃት ስሜት ተውጠን የራሳችንን አይሲስ – አረመኔውን ህወሓት – እንዳንረሳ ያሳስባል። መቆሚያው ለማይታየው የዜጎቻችን መሰደድ መንስኤዎች የነፃነት እጦት እና የኑሮ እድሎች መጥበብ መሆናቸው እንዳንዘነጋ ይጠይቃል። ንቅናቂያችን እነዚህ ተያያዥ ችግሮች ሁሉ የሚቃለሉት ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑባት ኢትዮጵያን ስንመሰረት ብቻ ነው ይላል። ለዚህም ደግሞ ሁላችንም በያለንበት የበኩላችንን ተሳትፎ ማድረግ ይገባናል። ሁለገብ ትግል ማለት፤ እያንዳንዱ ከሚመስለው ጋር እየተደራጀ በያለበት ወያኔ ማስጨነቅ፣ ማዋከብና ማዳከም፤ በመጨረሻም በጋራ ትግል ማስወገድ ማለት እንደሆነ ልብ እንበል። በሁለገብ ትግል ለውጥ የሚመጣው ሁሉም እንደ አቅሙ
በሚያደርገው ተሳትፎ በመሆኑ፣ የሚቻለንን በማድረግ የለውጥ ጠባቂ ሳንሆን፣ የለውጥ አምጭ አካል እንሁን ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
Source www.patriotg7.org

tirsdag 5. mai 2015

Election, Ethiopian Style

Since the last election, the ruling party has exerted more control and increased its repression of basic liberties.


There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent, writes Horne [Al Jazeera]
There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent, writes Horne [Al Jazeera]
This is what an election campaign looks like in Ethiopia, where the ruling coalition took 99.6 percent of parliamentary seats in the last national elections, in 2010.
Jirata, who asked that his real name not be used, is a 19-year-old student who was campaigning for a legally registered opposition party recently, when security officials arrested him.
They told him that he was working for a "terrorist group" that sought to forcibly bring down the government. He was badly beaten over the course of three nights and released on the condition that he end his involvement in politics. He is still limping from his injuries, and he told me he no longer has any interest in getting involved in politics. He says he will vote for the government party "because life is easier that way".
Ethiopia: Journalism under anti-terrorism law
Jirata was working for an Oromo party, representing an ethnic group long targeted by the government. But as Ethiopians go to the polls in late May, the prospects for opposition parties to fully and fairly campaign are grim.
Since the last election, the ruling party has only exerted more control and increased its widespread repression of basic liberties, including the rights to free expression, assembly, and association.
The courts provide no justice in cases of political importance. While election day is unpredictable, it's clear that the avenues by which opposition parties can fully function and citizens can engage on political issues are largely closed.
While there are 75 registered opposition groups, several of the largest parties have talked of boycotting the elections because of flawed electoral processes. Challenges with registering candidates, acquiring the funds they are legally entitled to, mobilising their supporters, and keeping their members out of prison have taken their toll.
In short, there is limited space for government critics to play a peaceful and constructive role.

Suppression of non-governmental voices
The Ethiopian media provides little coverage of relevant political issues ahead of the election since what vestiges of independent media existed have largely been eliminated since 2010.
Reporters critical of the government are regularly harassed, threatened and detained. In 2014 alone, over 30 journalists fled Ethiopia and at least six publications were closed down.
Sources providing information to media and human rights groups are regularly targeted. Many diaspora media websites, while heavily politicised, remain blocked in Ethiopia. Journalists must choose between self-censorship, harassment, imprisonment, and exile.
The situation hasn't been much better for opposition parties that want to organise peaceful protests and rallies ahead of the election. The Semayawi party (Blue Party), for example, is one of the newcomers in Ethiopia's electorallandscape, and since 2013 has tried to hold regular and peaceful issue-based protests.
Protesters and organisers have frequently been arrested and harassed, their equipment has been confiscated, and permits unfairly denied. One of their leaders is on trial on trumped-up terrorism charges.
The lone opposition parliament member is not running this time due to a split in his party, the Union of Democracy and Justice, in which Ethiopia's national electoral board played favourites. The net effect is that the government awarded the party name to an offshoot of the party that is more closely aligned to government policies and interests.
No dissent allowed
There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent or to contribute to the national political dialogue. Dissent of any type, particularly in rural areas, is dealt with harshly. The long-standing 5:1 system of grassroots surveillance - under which one individual is responsible for monitoring the activities of five households - has let local officials clamp down on dissent before it spreads beyond the household level.Telephone surveillance is commonplace, and the ongoing trial of a group of bloggers called Zone 9 has resulted in increased self-censorship online.
In short, there is limited space for government critics to play a peaceful and constructive role. The only international observers to the election will be the African Union. The European Union is not sending observers, noting that Ethiopia has not implemented recommendations by previous election observers. As Human Rights Watch documented after the 2010 elections, those who complain about election irregularities risk arrest and harassment.
"If we have an issue with government where do we go?" an Ethiopian who lives in a rural area recently told me, summing it up: "There is no media that will write our story, there are no more organisations that work on issues that the government does not like, if we take to the streets we are arrested, and if we go to their office to question we are called terrorists. If we go to the courts, there is no independence - we go to jail. There are no large opposition parties to vote for in the election, and even if there were, if we vote for them our lives then become very difficult. So what can we do? The elections are just another sign of our repression."
Source: Al Jazeera

søndag 3. mai 2015

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

fredag 1. mai 2015

የማዕከላዊ እዝ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መምጣቱ ታወቀ

mekononoch serawitየማዕከላዊ እዝ  ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መሄዱ ስላሳሰባቸው የእያንዳንዱን ወታደር ንብረት እየፈተሹ በርካታ ወታደሮችን ማሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ፣በምንጮቻችን መረጃ መሰረት የማዕከላዊ እዝ አመራሮች በየዕለቱ የሚከዳው የሰራዊት ቁጥር ስላሳሰባቸው ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ/ም የእያንዳንዱን ወታደር የግል ንብረት ሲፈትሹ የዋሉ ሲሆን በፍተሻውም ከ180 በላይ የሚሆኑት የሲቪል መታወቂያ ካርድ ያላቸው ወታደሮች መገኘታቸውን አስረድቷል፣
ይህ የተገኘው የሲቪል መታወቂያ ካርድም ከትውልድ ቦታቸው በተለያዩ መንገዶች የተላከላቸው ሲሆን ሲቪል መስለው ስርዓቱን እየጣሉ ለመሸሽ እንዲያግዛቸው የተዘጋጀ መሆኑን የገለፀው መረጃው በዚህ የተነሳም አራት ነባር የሰራዊት አባላቶች ለ3 ወር እስራት ተወስኖባቸው በአዲ ኮኮብ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፣
ምንጭ -ዴምህት

የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴ የሺሻ ማጨሻ ሆነ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ያስገነባው እና ዘመናዊ ተብሎ የሚጠራቅ ቀነኒሳ ሆቴል በሺሻ ማጨስ የተለከፉ ወጣቶች መጠራቀሚያ እና ጥራቱን ያልጠበቀ ስራ በመስራት የሚታወቅ ሆቴል ሆⶈል ። በአዲስ አበባ ከተማ ወጣት ሴቶች ከተለያዩ ጓደኞቻቸው ጋር የሚቀጣጠሩበት ዋነኛ መድረክ የሆነው ሺሻ ወይንም ሁካ ማጨሻ ስፍራዎች ሲሆኑ ፣በአሁን ሰአት ግን ይህ ሆቴል የሆቴሎች አስተዳደር ድርጅት እና የአዲስ አበባ ስራ እና ከተማ ልማት ቢሮ የሰጠውን፡ሕጝ፡ጥሶ የሺሻ ማጨሻ ሱቅ ማድረጉ በጣም አሳፋሪ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል ።
ቀነኒሳ በቀለ ሆቴሉን ካሰራ በሁዋላ የፊት ለፊት ገጹን የስሙን ጽሁፍ በቻይንኛ ማሰራቱ በሃገሩ ቋንቋ እና በማንነቱ የማይኮራ ነው ሲባል የተወቀሰ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ፣በሌላም በኩል ከፍተኛውን ስራ የሰሩት ቻይናዎች ሲሆኖ ጫና አሳድረውበት ነው ሲሉ ገልጸዋል ;በሌላም በኩል በአማካሪው ግፊት ነው የቻይንኛ ቋንቋ የመሰለ ፊደል ሊጠቀም የቻለው ሲሉም 

በተለይም እንደ አትሌት ቀነኒሳ አይነት የስፖርት ቤተሰብ የሆነ ሰው እና በህዝብ ዘንድ በስራው ገናናነትን ያተረፈው ድንቅ አትሌት ወጣቶችን ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠቡ መምከር ሲገባው በእራሱ ባሰራው ህንጻ ላይ ታዳጊ ወጣቶች እንዲበላሹ መጋበዙ አሳፋሪ እና ከእሱ ስራ እና ክብር የማይጠበቅ ነው ሲሉ ወርፈውታል ።
በሌላም በኩል ሆቴሉ የሚያቀርባቸው አግልግሎቶች ውስጥ ማናቸውም ከሁካ ወይንም ሺሻ ጋር የሚቀርቡ መጠጦችም፡ምግቦች ዋጋቸው የናረ ከመሆኑም በላይ መንግስት ያለቀረጥ የሚነግዱትን እንደሚያስር እና እንደሚቀጣ ሁሉ የአትሌት ቀነኒሳ ስራ ከማናቸውም ሆቴሎች ደረጃ በላይ ውድ መሆናቸው በላይም የመንግስት አስተዳደር ዝምታውን መምረጡ ተገቢ አይደለም ሲሉ አክለው ገልጸዋል ።
ሆኖም ግን በዚህ የሺሻ መሸጫ መደብር የሆነው የቀነኒሳ ሆቴል ውስጥ፡ባለ፡ስልጣናት እና የባለስልጣናት ልጆች ጊዜ ማሳለፊያቸው እና መዋያቸውንም ዘጋቢያችን ወይዘሪት ኢትዮጵያ ከስፍራው ገልጻለች ። ማለዳ ታይምስ

torsdag 19. mars 2015

በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግሰለቦች የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ ! ‹‹ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ የህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ›› አብርሃ ደስታ


በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግሰለቦች የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ
‹‹እኔ አሸባሪ አይደለሁም፡፡ ኢህአዴግ አሸባሪ ነው፡፡ ለሽብር ሀሳቡም ፍላጎቱም የለኝም›› ዳንኤል ሺበሺ
‹‹የተባለውን ለነገር አለማድረጌን ከእኔ በላይ የከሰሰኝ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል›› ሀብታሙ አያሌው
‹‹ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ የህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ›› አብርሃ ደስታ
‹‹ይሄ 19ኛ ችሎት የጦር ፍርድ ቤት ችሎት እየመሰለ ነው›› የሺዋስ አሰፋ
‹‹ሃይማኖቱንና ማኅበረሰቡን ከሚፈራ ህዝብ ወጥቼ እንዲህ አይነት ተግባር አልፈጽምም›› ባህሩ ታዬ
————————
ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2007 ዓ.ም፣ በከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙት እና በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ያሉ 10 ሰዎች ቀርበው ነበር፡፡ መዝገቡ ለዛሬ የተቀጠረው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ለመቀበል እና ከ1-5ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተከሳሾች በእስር ቤቱ ደረሰብን ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ላይ አስተያየት ካላቸው ለመቀበል መሆኑን የችሎቱ የግራ ዳኛ ገልጸዋል፡፡
የተከሰሾቹን የጽሑፍ አስተያየት በጠበቃ ተማም አባቡልጉ በኩል ቀርቦ ከመዝገብ ጋር ከተያያዘ በኋላ ተከሳሾቹ በየተራ የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ የግራ ዳኛው በመናገር 1ኛ ተከሳሽን ‹‹በክሱ ላይ እንደቀረበው ወንጀሉን ፈጽመሃል ወይስ አልፈጸምክም?›› ሲሉ ጠየቁት፡፡
ዘላለምም ‹‹አቃቤ ሕግ ባላደረኩት ነገር ህጉን መደገፍ ስለሚሆንብኝ ምንም መልስ አልሰጥም›› ሲል ዳኛው ‹‹በሥነ ሥርዓት ሕጉ ክሱን ክደው ተከራክራል› በሚል መዝግበነዋል›› በማለት መዝገብ ላይ አሰፈሩ፡፡
2ኛ ተከሳሽ አቶ ሃብታሙ አያሌው በበኩሉ ‹‹የተባለውን ለነገር (ሽብር) አለማድረጌን ከእኔ በላይ የከሰሰኝ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል፤ እረዳለሁም፡፡ አቃቤ ሕግ ለምን እንደከሰሰኝም አውቃለሁ፡፡ የቆምኩለትን ሕጋዊ ፓርቲንም አፍርሶታል፡፡›› ብሏል፡፡
3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺም ‹‹ሽብር የሚባለውን ነገር የሰማሁት ከሟቹ ኦሳማ ቢንላዳንና ከዘቶ መለስ ዜናዊ ነው፡፡ አደረክ ለተባልኩት ነገር ሃይማኖቴ፣ ዓላማዬ …አይፈቅድም፡፡ በዚህ ምክንያት ቤቴ እንዲወሰድ ተደርጓል፡፡ እኔ አሸባሪ አይደለሁም፡፡ ኢህአዴግ አሸባሪ ነው፡፡ ለሽብር ሀሳቡም ፍላጎቱም የለኝም፡፡ መንግሥት ፓርቲዬን ለማፍረስ የፈነቀለው …›› ብሎ ሳይጨርስ ፍርድ ቤቱ ንግግሩን እንዲያቋርጥ አስገድዶታል፡፡
4ኛ ተከሰሽ አብርሃ ደስታ መናገር ከመጀመሩ በፊት ‹‹ድርጊቱን መፈጸም አለመፈጸምህን ብቻ ተናገር›› ተብሎ ከችሎቱ ተነግሮት ነበር፡፡ አብርሃም በተረጋጋ መንፈስ ‹‹መልሱ እሱ አይደለም፤ የፈለኩትን እናገራለሁ፡፡ ሀሳቤን ልግለጽ›› ሲል ተናገረ፡፡ ዳኞች ሳይዋጥላቸው እንዲናገር ፈቀዱ፡፡ ‹‹ክሴ ከአሸባሪ ጋር በመገናኘት …የሚል ነው፡፡ አሸባሪ ለሚፈልገው ዓላማ ሰላማዊ ያልሆነ /ሰውን የሚጎዳ ድርጊት የሚያስፈጽም ነው፡፡ ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ ህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ …›› የግራ ዳኛው የአብርሃን ንግግር አቋረጡትና ‹‹ክሱ ላይ ህወሃት/ኢህአዴግ የሚል የለም፡፡ ክሱን መቃወም አለመቃወምህን ብቻ ተናገር›› አሉት፡፡ አብርሃም ‹‹ሕወሃት /ኢህአዴግ፣ ደህንነቱ ማፊያ ነው … ›› ዳኞቹ በድጋሚ አቋረጡት፡፡ አብርሃ ‹‹አልጨረስኩም›› ቢልም ዳኞቹ ከዚህ በላይ ሊሰሙት አልፈቀዱም፡፡
5ኛ ተከሳሽ የሺዋስ አሰፋም ‹‹ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ ነው የምናገረው፣ ስሙኝ›› ሲል ለችሎት ገለጸ፡፡ ዳኞቹ ክሱን መቃወም አለመቃወሙን ብቻ እንዲናገር ገለጹለት፡፡፡ የሺዋስ ‹‹ትንሽ ሁለት ደቂቃ የምትሞላ ንግግር ነች፡፡›› አላቸውና ቀጠለ፡፡ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 75/4 ላይ ልዩ ፍርድ ቤት ስለማቋቋም ይደነግጋል፡፡ ይሄ 19ኛ ችሎት የጦር ፍርድ ቤት ችሎት እየመሰለ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ ዳኞች ነጻ ስለመሆናቸው ይደነግጋል፡፡ የእኔ ችግር ችሎቱ ላይ ነው፡፡…›› ዳኞች የየሺዋስን ንግግር አቋረጡት፡፡ የሺዋስም ‹‹ዛሬ ብቻ ነው የምናገረው›› በማለት እንዲህ አለ፡- ‹‹በሕገ-መንግሥቱ ላይ ዳኞች ነጻ መሆን እንዳለባቸው ቢቀመጥም የመርማሪ እና ዐቃቤ ሕጎችን ሀሳብ ብቻ የሚሰማው፤ እኛን አይሰማ አሻንጉሊት ፍርድ ቤት ነው፡፡…›› የሺዋስም መናገር የቻለው ይሄን ብቻ ነው፤ ዳኞች ድጋሚ አስቁመውታል፡፡
6ኛ ተከሳሽ፣ ዮናታን ደግሞ ‹‹ያለፈቃድ እንድተውን እየተገደድኩ ነው›› ብሏል፡፡ 7ኛ ተከሳሽ (ስሙን የዘነጋሁት) ‹‹የተቀነባበረ ክስ ስለሆነ ምንም ማለት አልችልም፡፡›› ሲል 8ኛ ተከሻሽ ባህሩ ታዬም ‹‹ሃይማኖቱንና ማኅበረሰቡን ከሚፈራ ህዝብ ውስጥ ወጥቼ እንዲህ አይነት ተግባር አልፈጽምም፣ አለፈጸምኩምም፡፡ …ጊዜ እውነቱን ይፈርዳል›› ሲል ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 9ኛ እና 10ኛ ተከሳሾችም ‹‹ድርጊቱን አልፈጸምንም›› ብለዋል፡፡
ችሎቱም ‹‹ለአንድ ወር የለንም›› ካሉ በኋላ 15 የአቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለግንቦት 13፣ 14 እና 17 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡