
ከምስሉ የምትመለከቱት ከኣዲስ ኣበባ ቦሌ ኣለም ኣቀፍ ኤርፓርት ተነስቶ ኣሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የሚበረው ቦይንግ 777 መንገደኞች ኣውሮፕላን ነው። ከኣዲስ ዋሽንግተን የደርሶ መልስ ቲኬት ዋጋ 1600 (ኣንድ ሺ ስድስት መቶ ዩሮ) ነው። ይህ ማለት 2200 (ሁለት ሺ ሁለት መቶ በዶላር) ይሆናል በኛ ደግሞ 44,000 (ኣርባ ኣራት ሺ ብር) ማለት ነው። ገንዘቡ ኪስ የሚፈታተን ቢሆንም ለኢሃዴጋውያን ቀላልና እንደ ለገጣፎ መንገድ ቀን በቀን የሚመላለሱበት መንገድ ነው። ነፍሰጥሩ ተብላ የተሰየመችው ይቺ ኣውሮፕላን በየጊዜው ይዛ የምትሔደው የኢሃዴጋውያን ባለስልጣናት ሚስቶች ለመውለድ የደረሱ ሲሆን ይህ የሚያደርጉበት ምክንያት የማዋለጃ ሆስፒታል ፍለጋ ሳይሆን የሚወለደው ጨቅላ የኣሜሪካ ዜግነት እንዲኖረው ለማድረግ ብቻ ነው። ኢትዮጵያዊነት ክብር የማይሰጡት ኢሃዴጋውያን ባሁኑ ወቅት በኢኮኖሚና የውስጥ ችግር ቀን በቀን ቁል ቁል በመሄድ ላይ ያለችውን ኣገርና የህዝብን ጥያቄ መመለስ ኣቅሙና ብቃቱን ያጣ የሚመስለው የራሳቸውን ቤት በማሳመርና ከኣብራካቸው የወጣውን ደግሞ የወጪ ዜግነት እንዲኖረው በማድረግ ላይ እየተረባረቡ ይገኛል። በሃሰት ዲስኩርና ፕሮፓጋንዳ ተወጥሮ የሚሰራው ኢሃዴግ ወያኔ ብሩን ወደ ዶላር እየቀየረ ከኣገር በማስወጣት ላይ ይገኛል። ሁለት ልብ ሆኖ መኖር ያቀደ የሚመስለው ዛሬ በኣገር ውስጥ ሰውን እየገደለ በሌላ በኩል ደግሞ ወጪ ኑሮውን በማመቻቸት ጊዜው በልማት ወሬዎች ሸፋፍኖ ገመናውን ለመደበቅ እየጣረ ይገኛል። ይቺ ጃርት የበላው ዱባ የመሰለችው ኢትይጵያ በወያኔ ኣንገቱዋ ተሰብሮ እንዳትነሳና ኣንድ የብሄር ጎሳ ብቻ ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ ከፍተኛ ስራ ሰርተዋል እየተሰራም ይገኛሉ። ነገ ለምትፈርሰው ኣገራችንን ዛሬ ላይ ሆነን ካላመመን ነገ የምንቀበለው በልተው የተፉትን መሆኑን ኣንጠራጠር::