tirsdag 30. september 2014

የዋሽግተኑ ተቃውሞ ኢሳትን በዓለም ዓቀፍ ስመጥር የዜና አውታሮች ዝናው ገንኖ እንዲወጣ አደረገ፣ኤምባሲው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳውቆ እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ አራት ኪሎ ያለ ይመስል ዋሽግተንን በተኩስ መናጡ አሜሪካኖችን ማናደዱ አልቀረም (የዋሽግተኑን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተመለከተ የጉዳያችን አጭር ዘገባ)


ፎቶ www.csnwashigton.com 

''መሣርያውን ወደሚከራከሩት ሰዎች ደገነ እና ተኮሰ'' ''He points the weapon at others who argue with him and fires'' ሮይተርስ ከዋሽግተን ዲሲ ዛሬ የዘገበው። 

ዛሬ መስከረም 19፣2007 ዓም ዋሽግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተቃዋሚ ኢትዮጵያውያን ቁጥጥር ስር ውሎ ባለ ኮከቡ ሰንደቅ ዓላማ በነፃው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተቀይሯል። ተቃውሞውን አስመልክቶ ኢሳት ዘግይቶ በለቀቀው ተጨማሪ ዘገባ ተቃዋሚዎቹ በኢምባሲው ውስጥ ዘልቀው የአቶ አንዳርጋቸውን እና የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ይዘው ''ነፃነት! ነፃነት!'' ሲሉ አሳይቷል።

ቀደም ብሎ አምባሳደር ግርማ ብሩ በሸሚዝ እንደሆኑ ከሌሎቹ የኢምባሲው ሰራተኞች ጋር ቆመው ሲመለክቱም ሌላው የታየው ትዕይንት ነበር።ተቃውሞውን ተከትሎ የዓለም ስመጥር የዜና አገልግሎት ድርጅቶች ሮይተርስ እና የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ኤ ኤፍ ፒን ጨምሮ የቪድዮ ምንጫቸው ኢሳት የኢትዮጵያውያን ቴሌቭዥን መሆኑን ከመጥቀሳቸውም በላይ የኢሳትን ሰበር ዜና የያዘ ቪድዮ በቀጥታ ለጥፈው ታይተዋል።በመሆኑም በዛሬው እለት ኢሳት በመላው ዓለም የዜና አውታሮች የመወሳቱን ያህል ከእዚህ በፊት በእዚህ አይነት ስፋት በመላው ዓለም በሚገኙ ታላላቅ የዜና አውታሮች የተጠቀሰ አይመስለኝም።

በሌላ በኩል በአሜሪካን ሕግ ሽጉጥ ተኩሶ ማስፈራራት አይደለም በአንደበቱ ለማስፈራራት የሞከረ የሚደርስበት ቅጣት ከፍተኛ እንደሆነ ይታወቃል።ሆኖም ግን የኢምባሲው ሰራተኛ በተኮሰው ጥይት አካባቢውን በማሸበር እና በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ባሰሙ ዜጎችን በማስፈራራት ሕግ መጣሱን ለማወቅ ተችሏል።በአሁኑ ሰዓት ግን ግለሰቡ በቁጥጥር ስር መሆኑን በርካታ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እየጠቀሱ ይገኛሉ።ሆኖም ግን ግለሰቡ የዲፕሎማቲክ ከለላ ካለው አሜሪካ በአጭር ጊዜ ከሀገር እንዲወጣ ልታደርግ ትችላለች።በመሆኑም NBC የዜና አገልግሎት የተኮሰው የኢምባሲ  ሰራተኛ መታሰሩን ገልጧል።ዜናውን ይህንን በመጫን ማንበብ ይችላሉ።

ጉዳዩን ተከትሎ በነገው እለት ከኢትዮጵያ የሚወጣው  መግለጫ ይዘት ከወዲሁ መገመት አያስቸግርም።ሆኖም ግን ምንም አይነት መግለጫ እና ማብራርያ ቢሰጥ በአሜሪካውያንም ሆነ በምዕራቡ ዓለም ፅንሰ ሃሳብ አንፃር  ከጠቅላላ ጉዳዩ ውስጥ የኢምባሲ ሰራተኛው  ምንም አይነት የጦር መሳርያ  ባልያዙ በባዶ እጃቸው ተቃውሞ ባሰሙ ኢትዮጵያውያን ላይ  የጦር መሳርያ በመደገን የማስፈራራቱ እና በኃላም የመተኮሱን ያህል የጎላ እና አናዳጅ ነገር ነጥሮ አይወጣም። በመሰረቱ ዜጎች የሀገራቸውን ኢምባሲ ሲቃወሙ ይህ አዲስ አይደለም።እራሷ አሜሪካ የእራሷ ዜጎች ባልሆኑ ግን በሌሎች ሀገሮች ዜጎች ኤምባሲዋ ተውሯል።

በዲፕሎማሲው ዓለም ደግሞ አንድ ኢምባሲ በራሱ ሀገር ተወላጆች በተቃውሞ ቢናጥ ጉዳዩ የዓለም ዓቀፉን የቬና ስምምነት ከመመልከት  ይልቅ የአንዲት ሀገር የውስጥ ጉዳይ ገንፍሎ የመውጣት አይነተኛ አመላካች ጉዳይ ከመሆን አያልፍም።ከእዚህ በዘለለ ኢምባሲው ጉዳዩን ለፖሊስ ደውሎ እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ አራት ኪሎ ያለ ይመስል ዋሽግተንን በተኩስ መናጡ ነው አሜሪካኖችን የሚያናድደው።

በመጨረሻም አንድ ነገር ማንሳት ይቻላል።ባራክ ኦባማ ከአቶ ኃይለማርያም እና ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ቁጭ ብለው ካወሩ ገና  ሳምንት ሊሆነው ነው።የዛሬው በመዲናቸው ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተቃውሞ ያሰሙ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ለኦባማም ጭምር የሚያስደነግጥ ነው። የኦባማ የአፍሪካ ፖሊሲ ዕውን በጥናት ላይ የተመሰረተ ነው? ላለመሆኑ ማሳያው የዛሬው ጠንካራ ተቃውሞ ነዋ!

ጉዳያችን
መስከረም 20/2007 ዓም (ሴፕቴምበር 30/2014)

በህወሃት “የትግራይ ኩራት ተነክቷል” ባዮች አይለዋል

“ሃይለማርያም በቀጣዩ ምርጫ ሊታቀቡ ይችላሉ”

d t h

የሰሞኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ካቢኔያቸውን “ከኋላ” አስከትለው ከፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ያካሄዱት የፊት ለፊት ንግግር ያስደሰታቸውና ያስኮረፋቸው ክፍሎች አሉ። “በህወሃት መንደር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ የመወከል ባለጊዜው ህወሃት ነው። ህወሃት የኢትዮጵያ ምልክትና ተምሳሌት ነው” የሚሉት ወገኖች ቀደም ሲል ሲሰማ የነበረውን “የትግሬ ኩራት ተነክቷል” ስሜት በገሃድ ሲያንጸባርቁ ታይቷል።
አስገድደው ከሚመሩት ህዝብ ይልቅ ለውጪው ዓለም በመስገድና በማጎብደድ ወደር እንደሌላቸው የሚነገርረላቸው አቶ መለስ meles at g20ሰሞኑን አቶ ሃይለማርያም ያገኙትን ዕድል አላገኙም። ከታላቋ አሜሪካ መሪ ጋር በግል የፊት ለፊት ወግ አላደረጉም። በተለያዩ መድረኮች ላይ በጅምላ ተገኝተው ከመጨባበጥና ውስን ቃላቶችን ሲለዋወጡ ከመታየቱ ውጪ ያላገኙትን ይህንን ዕድል አቶ ሃይለማርያም ማግኘታቸው ቅር ያሰኛቸው ክፍሎች “መለስ ከመሬት በታች ሆነው የዲፕሎማሲውን ስራ ሰርተው መድረኩን እንዳመቻቹ አስመስለው በተለያዩ መንገዶች መግለጻቸው የዚሁ የኩራታችን ተነካ ስሜት ነጸብራቅ ነው” የሚሉ ወገኖች አሉ።
ስብሰባው በኋይት ሃውስ እልፍኝ ወይም በተባበሩት መንግስታት ሳሎን ውስጥ አልነበረም የተካሄደው። ዓለምአቀፉ ሒልተን በሚያስተዳድረው የኒውዮርኩ ዋልዶርፍ አስቶሪያ ሆቴል አንድ ክፍል ውስጥ የአሜሪካ “ባንዲራ” እና የኢህአዴግ አርማ እንዲሰቀል ተደርጎ ንግግሩ መደረጉን ያወሱ ክፍሎች፣ ፕሬዚዳንት ኦባማ ምርጫ እየተቃረበ መሆኑንን ጠቁመው “የሲቪል ማኅበረሰቡ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለበት መታየት አለበት” በማለት ያነሱት ሃሳብ ከስብሰባው በላይ ሚዛን አንስቷል። ኢህአዴግ የመያዶች ህግ በሚል በማተም የዘጋውን የሲቪል ማኅበረሰቡን ተሳትፎ አስመልክቶ ኦባማ ማንሳታቸው ውሎ አድሮ የሚመነዘሩ ጉዳዮችን እንደሚያስነሳ አመላክቷል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡካቸው የለጠፉት የዚሁ የሆቴል ክፍል ስብሰባ በርካታ አስተያየት ተሰንዝሮበታል። “ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር አንተ መሆን አለብህ” ከሚሉት የስጋና የደም አስተያየት ጀምሮ የዚሁ የፊት ለፊት ንግግር የቀድሞው “ባለ ራዕይ” መሪ “ራዕይ” ፍሬ አጎምርቶ የመታየቱ ብስራት ተደርጎ ተወስዷል፤ ታምኗል። ክብሩና ታሪኩም ለመለስ መቃብርና አጽም ህይወት ማላበሻ የአበባ ጉንጉን በረከት ሆኖላቸዋል።meles and hailemariam
የመለስ ሞት ዱብዳ የሆነበት ህወሃት፣ ከዱብዳው ማግስት ጀምሮ መርዶውን ሚስጥር ያደረገው የርዕሰ መንበሩ ወንበር ለይስሙላም ቢሆን እንዳይወሰድ አስፈላጊውን ዝግጅት ለማድረግ እንደሆነ በወቅቱ ብዙ የተባለበት ጉዳይ ነው። የመለስን የጥድፊያ ሞት “የግፍ ዋጋ፣ የአምላክ ቅጣት” በማለት ጮቤ የረገጡ ቢኖሩም፣ በህወሃት መንደር ግን ዜናው መሬት የተደረመሰ ያህል ስሜታቸውን ያራደ፣ ከሞት ጋር እልህ የተጋቡ የሚመስሉ፣ በዚሁ እሳቤ መለስ ቢሞቱም ያሉ ለማስመሰል የተደረገውና እየተደረገ ያለው ግብ ግብ “አምልኮ መለስ” ማስረጃ እንደሆነ ብዙዎች ተችተዋል።
ከዩኒቨርሲቲ የዲንነት በርጩማቸው ጀምሮ የሚያውቋቸው ሃይለማርያምን “የቆረጣ አካሄድን የተካነ” ሲሉ ይገልጹዋቸዋል። የሲዳማን ብሄረሰብ ለማስደሰት ከክልል ፕሬዚዳንትነታቸው ተነስተው አቶ መለስ ኢህአዴግ ቢሮ የተዛወሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም፣ በብሄር ውክልና ማመጣጠን ሰበብ ምክትል ጠ/ሚ ከመባላቸው ሌላ መለስ ቢሮ ለመጠጋት የሳቸው ሚና የለበትም። እንዳው አጋጣሚ ነው በሚል የሚከራከሩ ሃይለማርያም በኦባማ አስተዳደር ጫና ወንበሩን እንዲይዙ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ ህወሃቶች ውሳኔው “የትግሬዎችን ኩራት የነካ” መሆኑንን በመግለጻቸው በተደጋጋሚ መመከራቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ዲፕሎማቶች ይገልጻሉ።
ጎልጉል ቅርብ የሆኑ የአሜሪካ ዲፕሎማት ሰሞኑን እንደጠቆሙት ህወሃቶች “በኩራታችን ተወሰደ” ስሜት ሃይለማርያም ደሳለኝን በቀጣዩ ምርጫ በራሳቸው ሰው ለመተካት እየሰሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። በተለያዩ ሚዲያዎች ቴድሮስ አድሃኖም ቀጣዩ ጠ/ሚ/ር ይሆናሉ ስለመባሉ ለተጠየቁት “ቴድሮስ የግራውን መስመር የማያውቁ በመሆናቸው አምባገነን፣ ፈላጭ ቆራጭ መሪ ሊሆኑ አይችሉም፤ መስፈርቱን አያሟሉም በሚል ፈተናውን ሊያልፉ የማይችሉ ተደርገው ስለመወሰዳቸው መረጃው አለኝ” ብለዋል።
“የህወሃት የስለላው ማሽን” የሚባሉትና በፈላጭ ቆራጭነቱ አግባብ ግንባር ቀደም እንደሆኑ የሚነገርላቸው “ዶ/ር” ደብረጽዮን ሌላው እጩ ናቸው። ለመጀመሪያ ጊዜ ጎልጉል ስማቸውን ጠቅሶ ለጠ/ሚኒስትርነት ህወሃት ወደ ግንባር እያቀረባቸው መሆኑንን መግለጹ አይዘነጋም። የመረጃችን ምንጭ የሆኑት እኚሁ ዲፕሎማት፣ “ዶ/ር” ደብረጽዮን አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ በመሆን መስፈርቱን የሚያሟሉ ቢሆኑም ዓለምአቀፍ እውቅና የሌላቸውና ለዚያ የሚበቁ እንደማይሆኑ በራሳቸው በህወሃት ሰዎች መታመኑን ጠቁመዋል።haile fortune
በቀጣዩ ምርጫ ህወሃቶች ዋናውን “የኢትዮጵያ ውክልና” የሚባለውን ወንበር መልሶ የመያዝ እቅድ እንዳላቸው በቂ መረጃ አሜሪካ እንዳላት የጠቆሙት ዲፕሎማት፣ ከህወሃት ቁልፍ ሰዎች መካከል ሃይለማርያም ደሳለኝ ምክንያት ተፈጥሮ በቀጣዩ ምርጫ እንዳይወዳደሩ የማድረግ ዕቅድ ስለመኖሩ መስማታቸውን ጠቁመዋል። “ለጊዜው መረጃው ጥሬ ነው” ሲሉም ዝርዝር ውስጥ ለመግባት እንደማይችሉ አመልክተዋል።
የመለስ ሞት ይፋ በሆነበት ቅጽበት አቶ ሃይለማርያምን ከህወሃት እውቅና ውጪ ያነገሱት በረከት ስምዖን “የወንበሩ የወቅቱ ባለንብረት ህወሃት ነው” በሚሉት ክፍሎች ጥርስ ተነክሶባቸው እንደነበር ምንጭ እየጠቀሱ በርካታ ሚዲያዎች መዘገባቸው አይዘነጋም። በመተካካት ከኢህአዴግ መንበር ይወገዳሉ ወይም ተወግደዋል የሚባሉት አንጋፋ የድርጅቱ መሪዎች ጥላቸውና እጃቸው መዋቅሩን ነክሶ በመያዙ አሁንም በቀጣዩ ምርጫ የሃይለማርያም ጉዳይ በነዚሁ ሰዎች እጅ እንደሆነ የሚጠቁሙ አሉ።
ጎልጉል 

በአክሱም ዩኒቨርስቲ መምህር የሆነው የአንድነት ፓርቲ አባል ዩኒቨርስቲው ውስጥ ባሉ ካድሬዎች በደል እየተፈጸመብኝ ነው አለ

መምህር ብርሃነመስቀል ንጉሤ ዘውዴ በአክሱም ዩኒቨርስቲ መምህር ሲሆን በአዳማ የአንድነት ፓርቲ አባል ነው የመጀመሪያ ዲግሪውን በ2001 ዓ.ም ከአዳማ ዩኒቨርስቲ በፔዳጎጂካል ሳይንስ ሁለተኛ ዲግሪውን በ2004 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሂዩማን ሪሶርስ ኤንድ ኦርጋናይዜሽናል ዴቨሎፐመንት ኢን ኢዱኬሽን አግኝቷል፡፡
አስከፊውን የኢህአዴግ ሥርዓት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተቀላቀልኩት የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሳለሁ ነው:: በ1997 ዓ.ም በምስራቅ ሸዋ ናዝሬት የመኢአድ አባል ነበርኩ፣ በ1998 ዓ.ም በሰላማዊ የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎች የደረሰው ድብደባና አስራት በእኔም ደርሷል በማለት የገለጸው መምህር ብርሃነመስቀል፣ አሁን በአዳማ የአንድነት ፓርቲ አባል ሆኜ ዓመታትን አስቆጥሬያለሁ፡፡ በ1999 ዓ.ም አዳማ ዩኒቨርስቲ እንደገባሁ ተማሪውን የኢህአዴግ አባል ለማድረግ በየክፍሉ ባላቸው የሴል አመራር አባላት ተስፋ የቆረጡ ተማሪዎችን ወደኔ በመላክ እንዲጣሉኝ፣ በሃሰት እንዲወነጅሉኝ በማድረግ ከዩኒቨርስቲው እንድባረር የተለያዩ ሙከራዎች ቢደረግብኝም ፈጣሪ በሰጠኝ ብርታት በፔዳጎጂካል ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ በከፍተኛ ማዕረግ ለመመረቅ በቃሁ፡፡
በአዳማ ዩኒቨርስቲ አብረን ለ3 ዓመታት አንድ ክፍል ስንማር የነበረ የብአዴን የተማሪዎች የሴል አመራር የሆነ በመረጃ (ጆሮ ጠቢነት) ሥራ ተጠምዶ የነበረ ለከፍተኛ ተቋም መምህርነት ስንማር ያልነበረውን ውጤት ይዞ አክሱም ዩኒቨርስቲ ለመቀጠር የበቃው መምህር ስለሺ ጎሹ ገና ግቢውን እንደረገጠ ወደተሰጠው ሚሽን በመግባት እኔን የአካባቢው ተወላጅ ከሆኑት ጋር በማጋጨት እንድባረር ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ ዛሬ በመምህርነቱ ሳይሆን በመረጃ አቀባይነቱን ተጠቅሞ ከፖለቲካ ጋር በማያያዝና በመክሰስ ህልውናዬ አደጋ ውስጥ ወድቋል፡፡
አንድ መምህር እንደ መምህር ሊገመገም የሚገባው በቂ ዝግጅት አድርጎ መግባት፣ ኮርሱን በተመደበለት (በታለመለት) ጊዜ ገደብ መጀመርና መጨረስ፣ ተማሪውን ሊመዝን የሚችል አግባብነት ያለው ቴስት፣ ፈተና አሳይመንት በማዘጋጀት ተማሪውን መመዘን፣ ከሃይማኖት፣ ከፖለቲካ፣ ከአድልዎ የፀዳ ውጤት መስጠት እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ እስካሁን ድረስ መማርና ማስተማርን አስመልክቶ በመደበኛ፣ኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብር በሰጠኋቸው ኮርሶች ዙሪያ ምንም አይነት የፅሑፍና የቃል ቅሬታ በተማሪ ቀርቦብኝ አያውቅም፡፡
ከአዳማ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ አብረን ስንማር የነበረውን አሁንም በማስተማር ላይ ያለውን መምህር ስለሺ ጎሹን በግምገማ ጎድተኸዋል በሚል ቂም በመያዝ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆኔ ብቻ የሳይኮሎጂ ት/ት ስልጠና ሳይኖረኝ (ባልተቀጠርኩበት) ኮርስ በግድ እንዳስተምር መደረጉን በመቃወሜ ለማስተማር ፈቃደኛ አይደለህም በሚል ተወንጅያለሁ፡፡
መቼም ቢሆን እኔ በአቋሜ የፀናሁ ነኝ ኢህአዴግ አይደለሁም ብለሃል እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች በመፍጠር እንዲሁም ከታች እስከ ላይ ያሉ የግቢው የአመራር እርከን ላይ ካሉ አካላት ጋር በመተባበር በግቢው ውስጥ እኔን ከፖለቲካ ጉዳይ ጋር አገኛኝቶ ጥላሸት በመቀባት እንድገለል ተደርጌያለሁ፡፡
የህወሓት አባል ከሆነው መምህር ሰለሞን ብርሃነ ጋር በመሆን ከምመራው የፕሮግራም መሪነት ምንም ቅሬታ ሳይኖር በህገወጥ መንገድ እንድነሳ አድርገው ከእኔ ጋር ቅሬታ ውስጥ ያለውን የብአዴን አባል መምህር ስለሺ ጎሹን የፕሮግራሙ መሪ አደረጉ፡፡ እነዚህን በደሎች ጠቅሼ ለሶሻል ሳይንስ ቋንቋዎች ኮሌጅ ክስ ሳስገባ ክሴን ሳያዩት ለተከሳሾች ከለላና ሽፋን በመስጠት ክሴን ውድቅ አድርገው በተገላቢጦሽ ኦፊሺያል የመጨረሻ የፅሑፍ ማስጠንቀቂያ በግቢው በሚገኝ የማስታወቂያ ቦርድ ላይ በመለጠፍ የስም ማጥፋት ዘመቻ አድርገውብኛል፡፡ እነሱ ለሚፈፅሙትና እየፈፀሙ ላሉት Acadamic Crime or acadamic Corruption ክስ አስገብቼ ቢያንስ በ15 ቀን ውስጥ ውሳኔ ይሰጠው ቢልም እኔ ግንቦት 25 ቀን 2006 ዓ.ም ያስገባሁት ማመልከቻ እስከ ዛሬ ድረስ ሳይታይ ቆይቷል፡፡
ለምን ይግባኝና ክስ አስገባህ በሚል ሰበብም በአንድ ወር ከአሥር ቀን እንደገና ሁለተኛ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና የአንድ ወር ደሞዝ ተቀጣሁኝ፡፡ ይህ ሳያንስ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ስለጻፍንብህ በዚህ ዓመት ክረምት ላይ ስፔሻላይዝ ያደረኩበትን ሙያዬን ማለትም EpDM ኮርስ እንዳላስተምር አግደንሃል ብለው ስለከለከሉኝ ማግኘት የሚገባኝን 32 ክሬዲት ሃወር በብር ሲሰላ 32,000 (ሰላሳ ሁለት ሺህ) ብር እንዳጣ ተደርጌያለሁ፡፡ የሚደረግብኝን ተጽዕኖና በደል በዩኒቨርስቲ ውስጥ ለሚመለከታቸው የተቋሙ ቢሮዎችና እስከ ትምህርት ሚኒስቴር ድረስ ባመለክትም ምላሽ የሚሰጠኝ አካል አጥቼ የሞራል ውድቀት እንዲደርስብኝ ተደርጌያለሁ፡፡ ከእንግዲህም በኔ ላይ ምን ለማድረግ እንዳሰቡ ለማወቅ ተቸግሬያለሁ፡፡ እኔ ለዚህች አገር ዜጋ ነኝ እንደ መምህርነቴ የት/ት ጥራት ጉዳይ ያሳስበኛል፡፡ ይህ የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ ተደርጎ መወሰድ የለበትም፡፡ ሁላችንም እንደ አገር ማሰብ አለብን፣ በማለቴ እንደ ወንጀለኛ አስቆጥሮኛል፡፡ አሁንም ምን እንዳዘጋጁልኝ አላውቅም፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል መሆን አገር እንደመክዳት እየተቆጠረ ሰዎች አቅም እንዳይኖራቸው ከማህበረሰቡ እንዲገለሉ እየተደረገ፣ በካድሬዎች በደል እየደረሰበት፣ ከስራ እንዲሰናበት፣ በረሃብ ልመና ውስጥ እንዲገባ ተደርጎ የማያምንበትና የማይደግፈውን እንዲደግፍ እየተደረገ ነው በማለት መምህር ብርሃነመስቀል ንጉሤ ዘውዴ በምሬት ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጾዋል፡፡

onsdag 24. september 2014

ኣብራሃ ደስታን ኣላሰርኩም” የመቐለ ህወሓት (አምዶም ገብረስላሴ – ከትግራይ)

የትግራይዋ ህወሓት ማለቴ በሰማእታት ሓወልት ፅሕፈት ቤትዋ ያደረገችው ህወሓት( ኣዲስ ኣበባ የህወሓት ኣንጃ ሰላለች ነው) “ኣብራሃ ደስታ የታሰረበት ምክንያት ኣላውቅም” ኣለች።

ይህ ኑዛዜ የተሰማው በኣገር ደረጃ ለመንግስት ሰራተኞች እየተሰጠ ያለው ስልጠና የሚሉት(ተቃዋሚና ያለፉት ስርዓቶች የሚሰድቡበት መድረክ ስለመሰለ ነው) በትግራይ ክልል ፅህፈት ቤት(ደጀን ቢሮ) የሚሰሩ ሰራቶኞች በፕላኔት ሆቴል እየተካሄደ ባለው መድረክ ነው።

በዚህ መድረክ እየተነሱ ያሉት ጥያቄዎችና ሃሳቦች እጅጉን ጠንካሮችና የህወሓት ተራ ኣባላትና ጥቂት ፈላጭ ቆራጭ መሪዎች ፍፁም ታላቅ ልዩነት መነሩ የሚያሳዩ ናቸው።

በዚህ መድረክ “…ኣብራሃ ደስታ ህገ መንግስት የስጠው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብቱን በኣግባቡ በመጠቀሙ ለምን በሽብር ኣምካኝታቹ ኣሰራቹት?…” ለሚለው ጥያቄ ሲመልሱ ነው የመቐለዋ ህወሓት ኣብራሃን እንዳላሰረችና” የማሳሰርያው ምክንያትም ኣላውቅም” ብላ የካደችው።

ስብሰባው እየመሩት የነበሩት የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ “..ስለ ኣብራሃ ደስታ መታፈንና መታሰር በፌስቡክ ስሰማ በቀጥታ ወደ ህወሓት ቢሮ ሂጀ ኣነጋጋርኳቸው። ከህወሓት ፅህፈት ቤት ያገኘሁት መልስ ምንም የሚያውቁት እንደሌለና ህወሓት እንዳላሳሰረው ረግረውኛል..” ሲሉ በስብሰባው ገልፀዋል።

ኣብራሃ ደስታን የመቐለዋ ህወሓት ካላሳሰርችው ሌላዋ ተጠያቂ የኣዲስ ኣበባዋ የህወሓት ኣንጃ ናት ማለት ነው።

ከፍተኛ ቁጣ የተላበሰው የፕላኔት ሆቴል ተስብሳቢ ህዝብ ለህወሓት መሪዎች ኣስፈሪ ነበር።

ኣገሪትዋ እየበጠበጥዋት ያሉት መላ የህወሓት ኣባላት ሳይሆኑ የተወሰኑና ጥቂት ሰዎች መሆናቸው በግልፅ በመላ ትግራይ ያሉ ስብሰባዎች የተነሱ ሃሳቦች ቁልጭ ኣድረገው እያሳዩ ናቸው።

ሌላው ከፍተኛ የመወያያ ኣጀንዳ በዓረና ኣባላት እየደረሰ ያለው ዓፈና፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ ኣማራጭ ሃሳብ ወደ ህዝቡ እንዳይቀርብ ማደናቀፍ የኣዲስ ኣበባዋ ኣንጃ ሳትሆን የመቐለዋ ኣንጃ ስራ መሆኑ በግልፅ ተነግራቸዋል።

እጅጉን ያስደስታል ህዝቡ ነፃነት ፈልጓል፣ ዲሞክራሲን ናፍቆታል፣ መልካም ኣስተዳደርን ቋምጣል። ለዚህ ማሳያ በዓረና የሚደረገው የማፍረስ፣ እንዳይንቀሳቀስ የመከልከል ተግባር ውጉዝ ከመኣርዮስ እያለው ይገኛል።

tirsdag 23. september 2014

በቂሊንጦ ግንቦት 7 ነው ተብሎ የታሰረው ወጣት 10 ጥፍሮቹን ነቅለው እንዳሰቃዩት ተጋለጠ

የግንቦት 7 አባል ነው ተብሎ የታሰረው አበበ ካሴ የተባለ ወጣት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በሕወሓት/ኢሕአዴግ ካድሬ ወታደሮች ከፍተኛ የሆነ ግፍ እየተፈጸመበት መሆኑን ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ መረጃ ያደረሱ ወገኖች አስታወቁ።
“ዛሬ ከወደ ቂሊንጦ የደረሰኝ መረጃ እጅግ የሚዘገንና እንቅልፍ የሚነሳ ነው” በሚል መረጃውን ያቀበለን ውስጥ አዋቂ አበበ ካሴ ግንቦት 7 ነው በሚል የታሰረ ሲሆን መቀጣጫ እናደርግሃለን፤ ምስጢር አውጣ እያሉ በሚዘገንን መልኩ የ10 ጣቶቹን ጥፍሮች እንደነቃቀሉት አስታውቋል። እንደ መረጃ ምንጩ ገለጻ ከሆነ ብልቱ ላይ የታሸገ የላስቲክ ውሃ (ሃይላንድ) በማንጠልጠል ሲያሰቃዩት የቆዩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከብልቱ ፈሳሽ መውጣት መጀምሩም ተገልጿል። እንደመረጃ ምንጩ ገለጻ ከሆነ አበበ በብልቱ ላይ በደረሰበት ከፍተኛ ሕመም ህክምና እንዲደረግለት ቢጠይቅም “ሕክምና ማግኘት አይደለም ገና እንግድልሃለን” ብለው ከልክለውታል።
አበበ በአሁኑ ወቅት የእስረኛ መለያ መታወቂያውን መቀማቱን ያጋለጠው የመረጃ ምንጫችን የሚፈጸምበት ግፍ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ መምጣቱን እና እየተፈጸመበት ያለው የጭካኔ ተግባርም በምን ዓይነት ቋንቋ መግለጽ እንሚቻል ከባድ እንደሆነ ገልጾልናል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤክስፐርቶች ኢትዮጵያ ፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ትጠቀማለች ሲሉ ከሰሱ

-ተቃዋሚዎች ተገቢ ሪፖርት ብለውታል
United-Nations-01-300x220የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ሁሉን አቀፍ የአቻ ለአቻ ግምገማ የውሳኔ ሐሳቦችን ለመገምገም የተሰበሰበው የተመድ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ኤክስፐርቶች ቡድን መስከረም 8 ቀን 2008 ዓ.ም. በጀኔቭ ስዊዘርላንድ ባደረገው ስብሰባ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀረ ሽብረተኝነት አዋጁን ሐሳብን በነፃነት የመግለጽና የመደራጀት መብትን ለመጣስ መጠቀሙን እንዲያቆም አሳሰበ፡፡
ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ያቀረበችውን ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት አፈጻጸም ሪፖርትና የሰብዓዊ መብት ይዞታን በአገሪቱ ለማሻሻል የተወሰዱትን ሕጋዊና አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች ተከትሎ፣ አባል አገሮች የተለያዩ የውሳኔ ሐሳቦችን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡ ያደጉ አገሮች ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው እንዲሻሻል ወይም እንዲሰረዝ የጠየቁት ደግሞ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ነው፡፡
የፀረ ሽብርተኝነት ሕግና የሰብዓዊ መብት ጥበቃ፣ የመደራጀትና የሰላማዊ ስብሰባ፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የዳኞችና የጠበቆች ነፃነትና የኢሰብዓዊ አያያዝና ክብርን የሚያዋርድ ቅጣት መብቶች ልዩ ራፖርተሮች የሆኑት ቤን ኤመርሰን፣ ማይና ካያ፣ ዴቪድ ካዬ፣ ሚቸል ፎርስት፣ ጋብሪኤላ ክናውልና ጁአን ሜንዴዝ በጋራ ያወጡት ሪፖርት የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከኢትዮጵያ የወጡ ሪፖርቶች ማመላከታቸውን ይገልጻል፡፡ ‹‹ግርፋትና ኢሰብዓዊ አያያዝ በኢትዮጵያ ማቆያዎች ውስጥ መስተዋሉ ከፍተኛ የመሠረታዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፤›› ሲልም ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡
የኤክስፐርቶች ቡድኑ ሽብርተኝነትን መዋጋት አስፈላጊ ድርጊት ቢሆንም፣ ትግሉ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መሥፈርቶችን ሳይጣረስ መከናወን እንዳለበት ግን አስምሮበታል፡፡ ‹‹ፀረ ሽብርተኝነትን የሚደነግጉ አንቀጾች በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግጋት ውስጥ ግልጽ በሆነ ሁኔታ መተርጎም አለባቸው፡፡ ሕጎቹም ላልተገባ ዓላማ ጥቅም ላይ ሊውሉ አይገባም፤›› ሲልም ሪፖርቱ ያትታል፡፡
ሪፖርቱ በፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ የተከሰሱ ግለሰቦች ፍትሐዊ የሆነ የፍርድ ሒደት እያገኙ እንዳልሆነም ይወቅሳል፡፡ በተለይም ከሕግ አማካሪዎችና ከጠበቆች ጋር የመገናኘት መብት እንደማይተገበርም ያስረዳል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የሆነ የፍርድ ሒደት የማግኘት መብት፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትና የመደራጀት መብት በፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ አፈጻጸም መጣሳቸው ቀጥሏል፤›› ሲሉም ኤክስፐርቶቹ ያሳስባሉ፡፡
‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም በዘፈቀደ በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን ሁሉንም ሰዎች እንዲፈታ እንጠይቃለን፡፡ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና የሃይማኖት መሪዎች መደበኛና ሕጋዊ ሥራቸውን ያለ ዛቻና እስር ሳይፈሩ እንዲቀጥሉ ሊፈቀድላቸው ይገባል፤›› ሲሉም የተመድ ኤክስፐርቶች ጠይቀዋል፡፡ ኤክስፐርቶቹ ኢትዮጵያ የአዋጁን አፈጻጸም ከገባቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ግዴታዎች ጋር እያገናዘበች እንድታስኬድም ጥሪ አድርገዋል፡፡
የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን በመቃወም የሕዝብ ፊርማ እስከማሰባሰብ የደረሰው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ግዛቸው ሽፈራው (ኢንጂነር) ሪፖርቱን አስመልከቶ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹ፓርቲያችን አንድነት የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ የሕግ ሳይሆን የፖለቲካ ሰነድ ነው ያለው ከየትኛውም ፓርቲ ቀድሞ ነው፡፡ አዋጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ከኢሕአዴግ የተለየ አቋም የሚያንፀባርቁ ግለሰቦችና ጋዜጠኞችን ለማፈን ታሳቢ ተደርጎ የወጣ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አቶ ግዛቸው የሕጉን ተፅዕኖ በማየት ፓርቲያቸው በ2005 እና በ2006 ዓ.ም. ሕጉን ለማሰረዝ ፊርማ የማሰባሰብ ሥራ መሥራቱንም አስታውሰዋል፡፡
የተመድ ኤክስፐርቶች ሪፖርት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር ምን ያህል ጠቃሚ ነው በሚል የተጠየቁት አቶ ግዛቸው፣ ተመድ ሕጉ ጉድለት አለበት ስላለ ሳይሆን አዋጁ ከኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት ጋር የማይጣጣም በመሆኑ ፓርቲያቸው ተቃውሞውን እንደጀመረ ገልጸዋል፡፡ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብታቸው በሕገ መንግሥቱ ቢከበርም እነዚህን መብቶች በመጣስ በሕጉ አማካይነት በርካታ የህሊና እስረኞችን ኢትዮጵያ እንዳፈራችም አመልክተዋል፡፡ አዋጁ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጋጫል የሚሉ ከሆነ ለምን ጥያቄአቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ወይም ለሕገ መንግሥታዊ አጣሪ ጉባዔ እንዳላቀረቡ የተጠየቁት አቶ ግዛቸው፣ ከሕግ ክፍላቸው ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነና በቅርቡ እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል፡፡
እንደ አንድነት ፓርቲ ሁሉ በአዋጁ ላይ የሰላ ተቃውሞ በማቅረብ የሚታወቀው የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ይልቃል ጌትነት (ኢንጂነር) በበኩላቸው፣ የኤክስፐርቶቹ ሪፖርት የፓርቲያቸውን አቋም እንደሚያንፀባርቅ ገልጸዋል፡፡ ‹‹እንደ ፓርቲም እንደ ግለሰብም በሪፖርቱ በጣም ደስተኛ ነን፡፡ ኤክስፐርቶቹ ገለልተኛና በጉዳዮቹ ላይ ጥልቅ ዕውቀት ያላቸው ናቸው፡፡ ተዓማኒነት ያለው ሪፖርትም በማውጣት ይታወቃሉ፡፡ ይኼ ዲፕሎማሲያዊ ጫና ከመፍጠር አልፎ ተግባራዊ ዕርምጃ ለመውሰድም የሚያስችል ተፅዕኖ ይፈጥራል፤›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ከነሐሴ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ የፀናው የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 ተጠቅሶ በርካታ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተከሰው ፍርድ ያገኙ ሲሆን፣ በቅርቡም በቁጥጥር ሥር የዋሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በዚሁ አዋጅ ተከሰው ጉዳያቸው በመታየት ላይ ነው፡፡ መንግሥት ግን ይሠሩት ከነበረው ሙያዊ እንቅስቃሴ ባሻገር በሽብር ተግባር ሲሳተፉ እንደያዛቸው በመግለጽ ራሱን ይከላከላል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም የህሊና እስረኛ እንደሌለ መግለጻቸውን ባለፈው ረቡዕ ዕትም መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በአሁኑ የተመድ ኤክስፐርቶች ሪፖርት ላይ የመንግሥትን ምላሽ ለማግኘት ሪፖርተር ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

søndag 14. september 2014

በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈው መልዕክት ጽሑፍ

እንደምን አመሻችሁ!
በዚህች መላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከቤተሰቦቹና ከወዳጆቹ ጋር ሆኖ አዲሱን አመት ለመቀበል በሚዘጋጅባት ምሽት በግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስም እንኳን ለአዲሱ አመት በሠላም አደረሳችሁ ስል ከፍተኛ ክብርና ትልቅ ደስታ ይሰማኛል። መቼም በባህላችን ለሠላም ያለን ቦታ ከፍተኛ ስለሆነ አዲስ አመት በመጣ ቁጥር እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እንባባላለን እንጂ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሠላም ከጠፋ ብዙ አመታት ተቆጥረዋል።
ዉድ የአገሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ-
እኛን ለመሰለ ከሁለት አስርተ አመታት በላይ በዘረኛ አምባገነኖች ለተረገጠ ሕዝብ የአዲስ አመት ዋዜማ አሮጌዉን አመት ሸኝተን አዲሱን የምንቀበልበት የሆታና የጭፈራ ምሽት ሆኖ ማለፍ የሚገባዉ አይመስለኝም። ይልቁንም በዚህ አሮጌዉን 2006ትን ተሰናብተን አዲሱን 2007ትን በምንቀበልበት ምሽት ባሳለፍነዉ የትግል አመት የገጠሙንን ችግሮችና መሰናክሎች መርምረንና ከድክመታችን ተምረን በ2007 ዓም ለምናደርገዉ ወሳኝ ትግል እራሳችንን ማዘጋጀት ያለብን ይመስለኛል።
እኛ ኢትዮጵያዉያን ረጂም የነጻነት ታሪክና በየዘመኑ የዘመቱብንን ወራሪዎች በተከታታይ ያሸነፍን የጥቁር ሕዝብ የነጻነትና የአልበገር ባይነት ተምሳሌቶች ነን። ያለፉት ሃያ ሦስት አመታት ታሪካችንን ስንመለከት ግን እነዚህ አመታት እፍኝ በማይሞሉ የአገር ዉስጥ ጠላቶቻችን ተሸንፈን ክብራችንንና ፈጣሪ ያደለንን ነጻነታችንን ተቀምተን የኖርንባቸዉ አሳፋሪ አመታት ናቸዉ። በ1983 ዓም አምባገነኑን ደርግ በትጥቅ ትግል ያስወገዱት የወያኔ መሪዎች እነሱ እራሳቸዉ ከደርግ የከፉ አምባገነኖች ሆነዉ አሁንም ድረስ አገራችን ኢትዮጵያን እየገዙ ይገኛሉ።
የወያኔ ስርዐት በየቀኑ በአገርና በሕዝብ ላይ የሚፈጽመዉን ግፍ፣ በደልና ሰቆቃ ስርዐቱን አምባገነን ነዉ ብሎ በመጥራት ብቻ መግለጽ የሚቻል አይመስለኝም። አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ አለማችን ብዙ አምባገነን መንግስታትን አስተናግዳለች ዛሬም እያስተናገደች ነዉ። ወያኔ ግን እመራዋለሁ የሚለዉን ሕዝብና የሚመራዉን አገር በግልጽ የሚጠላ ከሌሎች አምባገኖች ለየት ያለ አምባገነን ነዉ። ወያኔ ሥልጣን ይዞ በቆየባቸዉ አመታት ሁሉ ኢትዮጵያዊነትን ሽንጡን ገትሮ ተዋግቷል፤ የኢትዮጵያን ደሃ ገበሬ አፈናቅሎ መሬቱን የኔ ለሚላቸዉ ታማኞቹና ለዉጭ አገር ቱጃሮች በርካሽ ዋጋ ሽጧል።ደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ሕዝብ ጋር ተግባብteዉ ይኖሩ የነበሩትን የአማራ ተወላጆች ይህ የእናንተ አገር አይደለም ብሎ ከገዛ አገራቸዉ ተፈናቅለዉ እንዲወጡ አድርጓል። በ 2005ና በ2006 ዓም በኦሮሚያ፤ በአማራ፤ በአፋርና በሶማሌ ክልሎች ከመሬታችን አታፈናቅሉን ብለዉ የመብት ጥያቄ ያነሱ አያሌ ሠላማዊ ዜጎችን በግፍ ጨፍጭፎ ገድሏል። ባጠቃላይ ወያኔ በዘር የተደራጀ፤ ሕዝብን በዘር የሚከፋፍልና የሚቃወመዉን ሁሉ በጅምላ እያሰረ በጅምላ የሚገድል ድርጅት ነዉ።
ይህም ሁሉ ሆኖ የወያኔ መሪዎች ከሕዝብና ከራሳቸዉ ጋር ታርቀዉ፤ በአገርና በሕዝብ ላይ የፈጸሙት ዝርፊያና ያደረሱት በደል በይቅርታ ታልፎ በኢትዮጵያ ዉስጥ እዉነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት የሚገነባበትን መንገድ እንዲያመቻቹ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደጋጋሚ ዕድል ሰጥቷቸዉ ነበር። ለምሳሌ ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ተቃዋሚ ድርጅቶች የምርጫዉ ዉጤት እንደተጭበረበረ እያወቁ የወያኔ አገዛዝ አገሪቱን ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ያለምንም ተቀናቃኝ እንዲመራና እነዚህን አምስት አመታት የተራራቀ ሕዝብን ለማቀራረብ፤ የዲሞክራሲ ተቋሞች መሠረት ለመጣልና አገራችን ዉስጥ መሪዎች በሀቀኛ ህዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደ ስልጣን የሚመጡበትን መንገድ ለማመቻቸት እንዲጠቀምበት ዕድል ተሰጥቶት ነበር። ከዚህ በተጨማሪ ተቃዋሚ ድርጅቶች እራሳቸዉም በዚህ አገርን የማዳን ጥረት ዉስጥ ሙሉ በሙሉ ከወያኔ ጎን በአጋርነት እንደሚቆሙና እንደሚተባበሩት ቃል ገብተዉለት ነበር። ሆኖም የወያኔ መሪዎች አስተዋይነትን እንደ በታችነት፤ ትዕግስትን እንደ ፍርሃት መቻቻልን ደግሞ እንደ ሞኝነት በመቁጠር በወዳጅነት ላቀረብንላቸዉ የአገራችንን እናድን ጥሪ ምላሻቸዉ እስር፤ ግድያና ከአገር እንድንሰደድ ማድረግ ብቻ ነበር።
በአገራችን በኢትዮጵያ አንድነትና በህዝባቿ የወደፊት ዕድል ላይ የተደቀነዉ መጠነ ሰፊ አደጋ ከወዲሁ የታያቸዉ የተለያዩ ኢትዮጵያዉያን በተለያየ መልኩ ከወያኔ ጋር ብዙ እልህ አስጨራሽ ድርድሮችን አካሂደዋል። ከዚህም አልፈዉ የኢትዮጵያ አንድነት የሚረጋገጥበትንና ህዝበቿ ሠላም፤ ፍትህና እኩልነት በነገሱበት አገር የሚኖሩበትን መንገድ ለማመቻቸት ከወያኔ መሪዎች ጋር ረጂምና አድካሚ መንገዶችን ተጉዘዋል። ሆኖም አገራችንን ከዉድቀት ለማዳን እነዚህን ሁሉ ተደጋጋሚ ጥረቶች ስናደርግ የወያኔ መሪዎች በግልጽ የነገሩን ነገር ቢኖር ፍላጎታቸዉና የረጂም ግዜ ዕቅዳቸዉ የኢትዮጵያን ሕዝብ አዋርደዉ መግዛት እንጂ ፍትህ፤ ነጻነት፤ ዲሞክራሲና እኩልነት በፍጹም አጀንዳቸዉ እንዳልሆነ ነዉ። የወያኔ መሪዎች ዕብሪትና ማን አለብኝነት በዚህ ብቻም አላበቃም፤ የጫኑብንን የባርነት ቀንበር አሜን ብላችሁ ተቀበሉ፤ አለዚያም ድፍረቱ ካላችሁና እኛ የመጣንበትን መንገድ የምትችሉት ከሆነ “መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ” ብለዉ አሹፈዋል።
የወያኔ መሪዎች ከ1997ቱ ምርጫ የተማሩት ትምህርት ቢኖር ኢትዮጵያ ዉስጥ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ቢኖር እነሱና ፓርቲያቸዉ በፍጹም ወደ ሥልጣን እንደማይመጡና ኢትዮጵያንም እንዳሰኛቸዉ መዝረፍ እንደማይችሉ ነዉ። ሰለሆነም ከምርጫ 97 በኋላ በነበሩት ሦስትና አራት አመታት የወሰዷቸዉ እርምጃዎች በሙሉ ነጻ ምርጫ የሚፈልጋቸዉን ተቋሞች የሚያሽመደምዱና ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን ባሰኛቸዉ ግዜ ሁሉ መወንጀል የሚያስችላቸዉ ህጎች ነበሩ ። ለምሳሌ የሜድያ ህግ፤ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ህግና የሽብርተኝነት ህግ የወያኔ መሪዎች የሚቃወማቸውንና ሀሳቡን በነጻነት የሚገልጸዉን ዜጋ ሁሉ ለመኮነን ያወጧቸዉ ህጎች ናቸዉ። እነዚህ ህጎች ከወጡ በኋላ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎቹ አንዱአለም አራጌና በቀለ ገርባ፤ ጋዜጠኛና መምህርት ርኢዮት አለሙና ሌሎችም ብዙ ሠላማዊ ዜጎች የግንቦት 7 አባላት ናችሁ በሚል ቃሊቲ ወርደዋል።
የወያኔ እስርና አፈና በአገር ዉስጥ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። የወያኔ አገዝዝ ከሱዳን፤ ከኬንያና ከጂቡቲ መንግስታት ጋር በመመሳጠር አያሌ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞችን ሽብርተኞች ናቸዉ እያለ አገር ቤት አስመጥቶ ሰቆቃ ፈጽሞባቸዋል። በመጨረሻም ባለፈዉ ሰኔ ወር አጋማሽ ዕብሪተኞቹ የወያኔ መሪዎች የንቅናቄያችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌን ፍጹም ህገወጥ በሆነ መንገድ አግተዉ እስከዛሬ ድረስ እያሰቃዩት ነዉ። እኛ የወያኔን መሪዎች እስሩን፤ ግድያዉን፤ ዝርፊያዉንና የዘረኝነት ፖሊሲያችሁን አቁማችሁ አገራችን ዉስጥ ፍትህ፤ሠላምና እኩልነት የሰፈነበት ስርዐት አንገንባ ብለን ስንወተዉታቸዉ እነሱ ግን አፈናቸዉንና ዉንብድናቸዉን በስደት የምንኖርበት አገር ድረስ ይዘዉ በመምጣት ለሰላም የከፈትነዉን በር ዘግተዋል። በዚህም የወያኔ መሪዎች እነሱ እራሳቸዉ በመረጡልን የትግል ስልት ገጥመናቸዉ ከአገራችን ምድር ጠራርገን ከማስወጣት ዉጭ ሌላ አማራጭ እንዳይኖረን አድርገዋል።
ዉድ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ!
የወያኔ አገዛዝ እኛን ኢትዮጵያዉያንን ያዋረደዉ አገር ዉስጥ ብቻ አይደለም። በዉጭ አገሮችም ባለቤትና ጠያቂ የሌለዉ ዜጋ አድርጎናል። በባዕድ አገሮች ጥቃት ሲደርስብን የራሱ ፓርቲ አባላት ወይም ደጋፊዎች ካልሆንን በዜግነታችን ምንም ነገር ለማድረግ ፈቃደኛ ሆኖ አያዉቅም። ዛሬ ከወያኔ ግፍና አፈና ለማምለጥ የሚሰደደዉ ኢትዮጵያዊ ከብዛቱ የተነሳ ቁጥሩ በዉል የሚታወቅ አይመስለኝም። የአፍሪካና የአረብ አገሮችን እስር ቤቶች የሞሉት ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ናቸዉ። ሴቶች እህቶቻችን አገር ዉስጥ የስራ ዕድል ስለማያገኙ በየአረብ አገሩ እየተሰደዱ የሚደርስባቸዉን ዉርደት በአፋችን ደፍረን መናገር ያቅተናል። ባለፈዉ አመት ከሳዑዲ አረቢያ ስንትና ስንት መከራና ፍዳ አይተዉ ወደ አገራቸዉ የተመለሱ ወገኖቻችን ሳዑዲ ይሻለናል እያሉ ለሁለተኛ ግዜ እየተሰደዱ ነዉ። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ የዛሬዋን ብቻ ሳይሆን የነገዋንም ኢትዮጵያ እገደለ መሆኑን ነዉ።
ዉድ የአገሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ!
የወያኔ ዘረኞች ባለፉት ሃያ ሦስት አመታት ያደረሰብንን በደል፤ ዉርደት፤ ስደትና ስቃይ ላንተ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ለሆንከዉ በዝርዝር መናገሩ የአዋጁን በጆሮ ነዉና አላደርገዉም፤ ሆኖም ይህ ስርዐት ምን ያክል ዘረኛ፤ ጨካኝና አረመኔ መሆኑን ማሳየት ስርዐቱን ንደን ለመጣል ለምናደርገዉ ወሳኝ ትግል ይጠቅማል ብዬ አጥብቄ ስለማምን ወያኔ ዛሬ በምንሰናበተዉ በ2006 ዓም ብቻ በሕዝብና በአገር ላይ የፈጸማቸዉን አንዳንድ ወንጀሎች መጥቀስ እፈልጋለሁ።
  1. የወያኔ የጸጥታ ሃይሎች የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችንን የአምልኮ ቦታቸዉ ድረስ ሰርገዉ በመግባት ለፈጣሪያቸዉ ፀሎት በማድረስ ላይ እንዳሉ በቆመጥ ደብድበዋል፤ አያሌ ምዕመናንን አስረዉ በሽብርተኝነት ከስሰዋle
  2. በመልካም ብዕራቸዉ ሕዝብን ከማስተማርና ከማሳወቅ ዉጭ ከሽብርተኝነት ጋር ቀርቶ ከተራ ወንጀል ጋር እንኳን የማይተዋወቁትን ዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ከሁለት ወር በላይ ያለ ማስረጃ በግፍ አስረዉ በቅርቡ በሽብርተኝነት ወንጀል እንዲከሰሱ አድርገዋል
  3. 2006 ወያኔ የለየለት የነጻ ፕሬስ ጠላት መሆኑን እንደገና ያረጋገጠበት፤ አያሌ ጋዜጠኞች የታሰሩበትና አገር ለቅቀዉ የተሰደዱበት፤አገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ የአለማችን ቀንደኛ የጋዜጠኞች ጠላት ተብላ የተሰየመችበት አመት ነዉ
  4. ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተዉን ሕዝብ ሳያማክሩ lezerefa endimechachew የአዲስ አበባን ከተማ የመሬት ይዞታ ለማስፋፋት የወሰዱትን እርምጃ በህጋዊ መንገድ የተቃወሙ ተማሪዎችን በጠራራ ፀሐይ በጥይት የጨፈጨፉትም በዚሁ በ2006 ዓም ነበር
  5. ወያኔ እራሱ የጻፈዉ ህገመንግስት የሰጣቸዉን መብት ተጠቅመዉ ሀሳባቸዉን የገለጹ አገር ዉስጥ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን ከሽብርተኞች ጋር ተባብራችኋል የሚል ሰንካላ ምክንያት ፈጥሮ አስሮ እያሰቃያቸዉ ነዉ
  6. ባለፈዉ አመት ወያኔ አንዱን ማህበረሰብ ከሌላዉ የማጋጨት እርምጃዎች በኦሮሚያ፤ ጋምቤላና ቤኒሻንጎል ወስዷል፤ በተለይ የአማራዊንና የኦሮሞን ህዝብ ማጋጨትን እንደ ቋሚ ስራዉ ወስዷል።
ዉድ ወገኖቼ! እነዚህ የዘረዘርኳቸዉ ወንጀሎች በሕዝብ ተመረጥኩ የሚለዉ ወያኔ በ2006 ዓም ከፈጸመብን ወንጀሎች በጣም ጥቂቶቹ ናቸዉ። የዛሬዉ ቁም ነገሬ ግን ወያኔ የፈጸማቸዉ ወንጀሎች ብዛትና ማነስ ላይ ማተኮር አይደለም። የዛሬዉ ቁም ነገሬ እንደ ሕዝብና እንደ አገር ለምን በገዛ መሪዎቻችን ወንጀል ይፈጸምብናል – እኛስ እስከመቼ ነዉ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ወንጀል በየቀኑ ሲፈጸምብን ዝም ብለን የምናየዉ? የሚለዉ መሠረታዊ ጥያቄ ላይ ነዉ።
በዚህ ምድር ላይ በዳይና ተበዳይ፤ አሸናፊና ተሸናፊ ነበሩ ለወደፊትም ይኖራሉ። ሲበደል በደሉን አሜን ብሎ ተቀብሎና ሁሌም ተሸናፊ ሆኖ የሚኖር አገርና ሕዝብ ግን በፍጹም የለም። በዛሬዉ ምሽት የኛ የኢትዮጵያዉያን ጀግንነት ድንበር ጥሰዉ ሊወርሩን በሚመጡ ጠላቶቻችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአገር በቀል ጠላቶችም ላይ መሆኑን በግልጽ ተነጋግረን መግባባት አለብን። ወያኔ ደግሞ አገር በቀል ጠላት ብቻ ሳይሆን ከወጭ ወራሪዎች ባልተናነሰ መንገድ የአገራችንን አንድነት የሚዋጋ ኃይል ነዉ። በ2007 ወጣቱ፤ ገበሬዉ፤ ሰራተኛዉና የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት እጅ ለእጅ ተያይዘዉ ይህንን አገር በቀል ጠላት ማስወገድ አለባቸዉ ብሎ ግንቦት ሰባት በጽኑ ያምናል።
ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔንና ወያኔ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት አስወግዶ ፍትህ፤እኩልነትና ዲሞክራሲን ለማስፈን በሚደረገዉ ህዝባዊ ትግል ዉስጥ ወጣቶች፤ ሴቶችና የመከላከያ ሠራዊት አባላት እጅግ በጣም ቁልፍ የሆነ ሚና ይጫወታሉ ብሎ ያምናል። ይህንን ደግሞ ወያኔም ስለሚረዳ ለዘረኝነት አላማዉ ከጎኑ ለማሰለፍ በጥቅማጥቅም የሚደልለዉና አለዚያም በሽብርተኝነት ፈርጆ እያሰረ የሚያንገላታዉ እነዚሁኑ ሦስት የህብረተሰብ ክፍሎች ነዉ።
የአገሬን ዳር ድንበር ከወራሪዎች እጠብቃለሁ ብለህ የመከላያ ሠራዊቱን የተቀላቀልክ የአገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆይ! አንተ የለበስከዉ ዪኒፎርም ጀርባህ ላይ ተቀድዶ ፀሐይና ብርድ ሲፈራረቁብህና የወለድካቸዉ ልጆችህና የወለዱህ እናትና አባትህ ደግሞ የሚላስና የሚቀመስ አጥተዉ በችግር አለንጋ ሲገረፉ፤ በየክልሉ እየሄድክ የገዛ ወገኖችህን እንድትገድል ትዕዛዝ የሚሰጡህ የወያኔ አለቆችህ ግን በኮንትሮባንድና በግልጽ የመሬት ዝርፍያ በዋና ዋና የአገራችን ከተሞች ከገነቧቸዉ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ዉጭ ካንተና ከሕዝብ የዘረፉት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ትላልቆቹን የዉጭ አገር ባንኮች አጨናንቋል። አንተና ቤተሰቦችህ ነገ ምን እንሆናለን የሚል የችግር እንባ ስታነቡ ጥጋበኞቹ አለቆችህ ግን የጥጋብ ግሳት ያገሱብሃል።
ዉድ የአገሬ መካላከያ ሠራዊት አባል ሆይ!
ምትክ የሌላትን አንድ ህይወትህን ልትሰጣት ቃል በገባህላት አገር ዉስጥ እንዲህ አይነቱ የሚዘገንን በደል ባንተና በወገኖችህ ላይ ሲፈጸም ዝም ብለህ የምትመለከትበት ግዜ ማብቃት አለበት። መጪዉ አዲስ አመት ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ የገባዉን ቃል ተግባራዊ ማድረግ የሚጀምርበት አመት ነዉ። ይህንን መከላከያ ሠራዊቱን ጨምሮ መላዉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ባርነት ነጻ የሚያወጣ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምረን ከወያኔ ጋር ትንቅንቅ ዉስጥ ስንገባ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ከታጠቁት መሳሪያ ጋር ወደምንገኝበት ቦታ ሁሉ እየመጡ እንዲላቀሉንና በምንም ሁኔታ የዘረኞችን ትዕዛዝ ተቀብለዉ በገዛ ወገኖቻቸዉ ላይ ክንዳቸዉን እንዳያነሱ በግንቦት 7 ንቅናቄ ስም አገራዊ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ከእያንዳንዱ መቶ የአገራችን ሕዝብ ዉስጥ 64ቱ ዕድሜዉ ከ25 አመት በታች ነዉ፤ወያኔ እርስ በርሱ እንዳይገናኝ፤ አንዳይደራጅና በአገሩ ጉዳዮች ላይ እንዳይወያይ አፍኖ የያዘዉ ይህንኑ የአገራችን የወደፊት ተስፋ የሆነዉን ወጣት ነዉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በሚገባ በእዉቀት ተኮትኩቶ ካደገ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ተረክቦ አገሩን ከድህነትና ከኋላ ቀርነት ያላቅቃል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ የmiጣለበትም ይሄዉ ወጣት ነዉ። ሆኖም ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንቶች በግልጽ እንዳየነዉ ወያኔ የአገሪቱን ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የራሱን የከሰረ አስተሳሰብ ማስፋፊያና የፓርቲ አባላት መመልመያ ጣቢያ አድርጓቸዋል። በተለይ በአሁኑ ወቅት በእረፍት ላይ የሚገኙትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለሥልጠና ካልመጣችሁ ወደ ትምህርት ገበታችሁ መመለስ አትችሉም ብሎ እያስፈራራ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ መማር ያለባቸዉን ተማሪዎች ተራ የካድሬ ስልጠና እየሰጣቸዉ ነዉ።
በየዘመኑ የተነሳዉ የኢትዮጵያ ወጣት አገሩን ከወራሪዎች በመከላከልም ሆነ የአገር ዉስጥ ፈላጭ ቆራጭ የገዢ መደቦችን ፊት ለፊት በመጋፈጥ የረጂም ዘመን አኩሪ ታሪክ ያለዉ ወጣት ነዉ። እኔ በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ ያለኝ እምነት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ፤ የዚህ ትዉልድ ወጣትም የወያኔን ዘረኞች የገቡበት ገብቶ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ የእናት አገሩን አንድነትና የወገኖቹን ነጻነት ያስከብራል።
ዉድ የአገሬ ወጣቶች – መጪዉ አዲስ አመት እስከዛሬ ያጎነበሰዉን አንገታችንን ቀና አድርገንና ከዳር እስከ ዳር ተደራጅተን ወያኔን በህዝባዊ እምቢተኝነና በህዝባዊ አመጽ ከስልጣን ለማስወገድ ወደ ወሳኙ ፊልሚያ የምንገባበት አመት ነዉ። ወያኔ ስልጣን እንደያዘ በቆየ ቁጥር ከማንኛዉም የህብረተሰብ ክፍል በላይ ተስፋዉ የሚደበዝዘዉና የወደፊት ኑሮዉ የሚጨልመዉ ያንተ የወጣቱ ትዉልድ ነዉና ወያኔ ለራሱ ጥቅም የፈጠረልህን አደረጃጀት በመጠቀም ከምታምናቸዉ ጓደኞችህ ጋር ሆነህ እራስህን አደራጅ፤ የነጻነት ሃይሎች ለሕዝብ የሚያሰራጯቸዉን መረጃዎች በየቀኑ ተከታተል፤ የወያኔን ዕድሜ የሚያሳጥሩ እርምጃዎችንም በያለህበት አካባቢ መዉሰድ ጀምር። በዚህ መራራ ትግል ዉስጥ ያንተ የወጣቱ ትዉልድ ትልቁ ጉልበት መደራጀትህና በድርጅታዊ ዲሲፕሊን መታነጽህ ነዉና እነዚህ ሁለት እሴቶች ምን ግዜም እንዳይለዩህ።
ዉድ የአገሬ ወጣት!
ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ስራ የሚያስገኘዉ ትምህርትና ችሎታ ሳይሆን የወያኔ ድርጅቶች አባል መሆን ነዉ፤ እሱ ደግሞ እራስን መሸጥ ነዉና ኢትዮጵያዊ ስለሆንክ ብቻ እንደማታደርገዉ እርግጠኛ ነኝ። ያለ የሌለ ጥሪትህን አፍስሰህ ንግድ ልጀምር ብትልም መንገዱን ይዘጉብሃል ወይም አብዛኛዉን ትርፍህን ለወያኔ ሙሰኞች ካልገበርክ መነገድ አትችልም ይሉሀል። እneዚህን የጠቀስኳቸዉን ሁለት ፍትህ አልባ አሰራሮች ተቃዉመህ አደባባይ ስትወጣ ደግሞ የአግዓዚ አልሞ ተኳሾች ደረት ደረትህን ይሉሀል። ከዚህ ሁሉ ዉጣ ዉረድ በኋለ ያለህ አማራጭ ወይ ለወያኔ ዘረኞች እየሰገድክ መኖር አለዚያም እናት አገርህን ጥለህ መሰደድ ነዉ። እስከዛሬ የተንገላታኸዉ፤ የታሰርከዉ፤ የተገረፍከዉና የጥይት እራት የሆንከዉ ዉድ የአገሬ ወጣት ሆይ – በዚህ አዲስ አመት ዋዜማ ግንቦት 7 ላንተ፤ ለቤተሰቦችህና ለአገርህ የሚበጅ ሦስተኛ አማራጭ ይዞልህ መጥቷል። ከአገርህ አትሰደድም፤ ለወያኔ ዘረኞችም እየሰገድክ አትኖርም ! ወያኔን ፊት ለፊት ተጋፍጠህ አንተንም ወገኖችህንም ነጻ ታወጣለህ። ገና ዋና ዋና ስራዉን ሳይጀምር መኖሩን በማሳወቁ ብቻ ወያኔን ያርበደበደዉ የሕዝባዊ አመጽ ኃይል ዬት እንዳለ ታዉቃለህና በትናንሽ ቡድኖች እራስህን እያደራጀህ ዛሬ ነገ ሳትል ናና ተቀላቀለን። ለግዜዉ ወደ ጫካዉና ወደ ዱሩ መጥተህ መቀላቀል የማትችለዉ ደግሞ ወያኔን በዝቅተኛ ወጪ በፍጥነት ማስወገድ የምንችለዉ ከዉስጥም ከወጭም ስናጣድፈዉ ነዉና የነጻነት ኃይሎች በተከታታይ የሚሰጡህን መረጃ በመከተል እራስህን አደራጅተህ በየአካባቢህ የወያኔ ስርዐት የቆመባቸዉን መሠረቶች አፍርስ።
ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
የአዲስ አመት ዋዜማ እንደ ግለሰብ በአሮጌዉ አመት በዕቅድ ይዘን ያላከናወንናቸዉን ቁም ነገሮች በአዲሱ አመት ለማከናወን ለራሳችን ቃል የምንገባበት፤ እንደ መሪ ደግሞ ለሕዝብና ለአገር አዲስ ራዕይና አዲስ ተስፋ የምንፈነጥቅበት፤ ከስህተታችን የምንታረምበትና ጠንካራ ጎናችንን ይበልጥ የምናጎለብትበት መልካም አጋጣሚ ነዉ። በዚህ አዲስ አመት ከሃያ ሦስት አመት ስህተታቸዉ ታርመዉና የበደሉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀዉ የፍትህና የነጻነት ትግላችንን አንዲቀላቀሉ የትግል ጥሪ የምናደርግላቸዉ ብዙ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ አራት ድርጅቶችን ያቀፈዉ ኢህአዴግ የሚባለዉ ድርጅት ነዉ። ወገናችንን እንጠቅማለን ብላችሁም ሆነ በሌላ ሌላ ምክንያት ከጠላታችሁ ከወያኔ ጋር የተቆራኛችሁ የኦህዴድ፤ የባዕዴንና የደኢህዴግ አባላትና መሪዎች ሁሉ በዚህች የአዲስ አመት ዋዜማ ምሽት የበደላችሁትን የኢትዮጵያን ሕዝብ የምትክሱበት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩን ሳብስርላችሁ እጅግ በጣም ደስ እያለኝ ነዉ። ልቦና ያላቸዉ ወገኖች በህወሓትም ዉስጥ ይኖራሉ ብለን እናምናለን። ህወሓትን ለቆ ለመዉጣትም የመጨረሻዉ ሰዐት ደርሷልና አሁኑኑ እየለቀቃችሁ ዉጡ። ለአገራቸዉ አንድነትና ዲሞክራሲያዊ እኩልነት የሚታገሉት የደሚሂት ወንድሞቻችን ከሌሎች ወገኖች ጋር አብረዉ እየታገሉ ነዉ። ለሀቅና ለእኩልነት ብለህ ወያኔን የተቀላቀልክ ታጋይ በሙስና የተጨማለቁ ወራዳ መሪዎች ጀሌ መሆንህ ማብቃት አለበት።
በኢህአዴግና በሌሎቹም የወያኔ አጋር ድርጅቶች ዉስጥ የምትገኙ ዉድ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ – እስከ ዛሬ እራሱን “የትግራይ ሕዝብ ነጸ አዉጭ ግንባር” እያለ የሚጠራዉ ድርጅት ጥቂት ዘራፊ መሪዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ከሃያ አመታት በላይ ረግጦ መግዛት የቻለዉ በቅርጹ ኢትዮጵያዊ በይዘቱ ግን ፍጹም ፀረ ኢትዮጵያ የሆነ ድርጅት ፈጥሮ መንቀሳቀስ በመቻሉ ነዉ። “የአገሩን ሠርዶ በአገሩ በሬ” እንደሚባለዉ ወያኔ “ኢህአዴግ” በሚል ሽፋን የኦሮሚያን፤ የአማራንና የደቡብ ሕዝብ ክልሎችን ተቆጣጥሮ አገራችንን መዝረፍ ባይችል ኖሮ የኢትዮጵያን ሕዝብ እንኳን ሃያ ሦስት አመት አንድ ወርም ተደላድሎ መግዛት አይችልም ነበር። ስለዚህ ከዚህ የሕዝብና የአገር አንድነት ጠላት ከሆነዉ ድርጅት እራሳችሁን እያገለላችሁ ህዝባዊ ትግሉን እንድትቀላቀሉና የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማይቀረዉ ድል እንድታበቁት በዚህ ጀግና ሕዝብ ስም እማፀናችኋለሁ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ታታሪ ሠራተኛ ሕዝብና ለሌሎች የሚተርፍ ለምለም አገር ይዘን ዛሬም ስማችን የሚጠቀሰዉ ከድህነት፤ ከኋላ ቀርነትና ከሰብዓዊ መብት ረጋጮች ተርታ ነዉ። ወያኔ ገነባሁ ብሎ የሚነግረን የኃይል ማመንጪያ ግድቦች ብዛት እንኳን ለኛ ለጎረቤቶቻችንም የሚተርፉ ናቸዉ። ነገር ግን አብዛኛዉ የከተማ ነዋሪ በሳምንት ከአንድ ግዜ በላይ መሠረታዊ የመብራት አገልግሎት አያገኝም፤ እራሱን ልማታዊ መንግስት እያለ የሚጠራዉ ወያኔ የአገሪቱ ኤኮኖሚ በድርብ አኀዝ እያደገ ነዉ ማለት ከጀመረ አስር አመታት ተቆጥረዋል፤ ሆኖም የአገራችንና የአፍሪካ መዲና የሆነችዉና ወደ አራት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ የሚኖርባት አዲስ አበባ የዉኃ ያለህ እያለች መጮህ ከጀመረች አመታት ተቆጥረዋል። የወያኔ መሪዎች ይህንን ግዙፍ ማህበረሰባዊ ችግር እያወቁ ችግሩን ለመቅረፍም ሆነ በየቀኑ እያደገ ለሚሄደዉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የመጠጥ ዉኃ ዘላቂ ዋስትና ለመስጠት የሰሩት ወይም ያቀዱት ምንም ነገር የለም።
ወያኔ የተከተላቸዉ ብልሹ የኤኮኖሚ ፖሊሲዎች አገራችን ዉስጥ የሸቀጥ ዋጋ በየቀኑ እንዲያድግ አድርጓል። ይህ የዋጋ ንረት የፈጠረዉ የኑሮ ዉድነት ደግሞ ወላጆች ልጆቻቸዉን በፈረቃ እንዲመግቡ ከማስገደዱም በላይ በአዲስ አበባና በሌሎቹም ከተሞቻችን ለወትሮዉ የፍቅርና የመቀራረብ ምልክት የነበረዉ ጉርሻ ዛሬ በችርቻሮ የሚሸጥ ሸቀጥ ሆኗል። ኢትዮጵያ ዉስጥ ዕንቁጣጣሽ የሚከበረዉ ቅርጫዉ፤ በጉና ዶሮዉ ተገዝቶ ከቤተሰብና ከወዳጅ ዘመድ ጋር አንድ ላይ በመሆን ነበር፤ ዛሬ ግን የኑሮ ዉድነቱና የዋጋ ንረቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትላልቅ አመት በአሎቹን ከባህሉና ከወጉ ዉጭ በባዶ ቤት ለብቻዉ እንዲያከብር አስገድዶታል።
ግብር ከፋዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህ ሁሉ ችግርና መከራ እየተፈራረቀበት የወያኔ ሹማምንትና ምስለኔዎቻቸዉ ግን በፎቅ ላይ ፎቅ ይሰራሉ፤ የቅንጦት መኪና በየአመቱ ይቀያይራሉ ወይም ቅምጥል ልጆቻቸዉን በሕዝብ ገንዘብ አዉሮፓና አሜሪካ እየላኩ ያስተምራሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀላሉ ሊወገዱ በሚችሉ በሽታዎች አንደ ቅጠል እየረገፈ እነሱና ቤተሰቦቻቸዉ ግን ጉንፋን በያዛቸዉ ቁጥር በሕዝብና በአገር ገንዘብ አዉሮፓና አሜሪካ እየሄዱ ይታከማሉ። ይህ ሁሉ በሕዝብ ላይ የሚያደርሱት በደል አልበቃ ብሏቸዉ በየከተማዉ ቤቶችን እያፈረሱ መሬቱን እነሱ ለሚፈልጉት ባለኃብት ይሸጣሉ። ዉድ የአገሬ ሕዝብ – ለመሆኑ እስከመቼ ነዉ በገዛ አገራችን እፍኝ በማይሞሉ ሰዎች እንደዚህ እየተዋረድን የምንኖረዉ? እስከመቼ ነዉ እነሱ ልጆቻችንን እየገደሉ እኛ እየቀበርን የምንኖረዉ? እስከመቼ ነዉ ግብር ከፋዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ደሞዝ በሚከፍላቸዉ ሰራተኞቹ እየተናቀ፤ እየተዋረደ፤ እየታሰረ፤ እየተገደለና ከአገሩ እየተሰደደ የሚኖረዉ? ለመሆኑ ኢትዮጵያ የነማን አገር ናት? እኛስ የነማን ልጆች ነን?
ዉድ አባቶቼ፤ እናቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ -
እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለእነዚህ ጥያቄዎች ተገቢዉን ምላሽ የሚሰጥበት ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ፊት ለፊታችን ተደቅኗል። 2007 እንደሌሎቹ አመቶች “ዕንቁጣጣሽ በያመቱ ያምጣሽ” ብለን ተቀብለን የምንሸኘዉ አመት አይሆንም፤ መሆንም የለበትም። ነገ የምንቀበለዉ አዲስ አመት ሲገድሉን ዝም ብለን የማንሞት፤ ሲያሳድዱን አገራችንን ትተንላቸዉ የማንሰደድ፤ ሲንቁንና ሲያዋርዱን ደግሞ ክብር፤ ልዕልናና የረጂም ግዜ ታሪክ ያለን ታላቅ ሕዝብ መሆናችንን ለጠላትም ለወዳጅም የምናረጋግጥበት አመት ነዉ። ይህ አመት የአገራችንን የፍትህ፤ የደህንነትና የመከላከያ ተቋሞች እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመ ሲያስረን፤ ሲያዋርደንና ሲገድለን የከረመዉን ዘረኛ አገዛዝ ለማስወገድ ተግባራዊ እርምጃዎችን መዉሰድ የምንጀምርበት የድልና የመስዋዕትነት አመት ነዉ። ይህ አመት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ከወያኔ ጋር በሚደረገዉ የነጻነት ትግል ዉስጥ የኔ ድርሻ ምንድነዉ የሚለዉን ጥያቄ እራሱን ጠይቆ መልሱንም እሱ እራሱ የሚመልስበት አመት ነዉ። ነጻና ፍትሃዊ በሆነችዉ ኢትዮጵያ የሚጠቀመዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ሁሉ ኢትዮጵያን ነጻና የእኩሎች አገር ለማድረግ በሚደረገዉ ትግልም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ አለበት።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ወያኔዎችን በድርድር ሞከርናቸዉ፤ በምርጫ ሞከርናቸዉ በሠላማዊ መንገድም በሁሉም አቅጣጫ ሞከርናቸዉ፤ ለእነዚህ ሁሉ ሙከራዎቻችን የሰጡን ምላሽ አርፋችሁ ተገዙ፤ ትታሰራላችሁ ወይም ኢትዮጵያን ለቅቃችሁ ዉጡ የሚል የዕብሪትና የንቀት መልስ ነዉ። ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከሎሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን አንገዛም፤ ከህግ ዉጭ አንታሰርም፤ አገራችንንም ለቅቀን አንወጣም የሚል ጽኑ አላማ አንግቦ ታግሎ ሊያታግላችሁ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ኑና ተቀላቀሉኝ እያለ ነዉ ። ንቅናቄያችን የኢትዮጵያን አንድነት፤ ሠላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወያኔ ስርዐት መወገድ አለበት ብሎ ያምናል፤ ይህ እምነታችን፤ ለእናት አገራችን ኢትዮጵያ ያለን ፍቅርና፤ የነጻነት ጥማታችን ወደትግሉ ሜዳ እንድንገባ አድርጎናል። ይህ ትግል ወያኔን ለማስወገድ ብቻ የሚደረግ ትግል ሳይሆን የተረጋጋ፤ ጤናማና በዲሞክራሲ መሠረቶች ላይ የቆመ አስተማማኝ የፖለቲካ ስርዐት ለመፍጠርም ጭምር የሚደረግ ትግል ነዉ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ማለት የሚገባንን ሁሉ ብለን ጨርሰናል፤ ካሁን በኋላ ማድረግ የሚገባንን ሁሉ ማድረግ አለብን። ሁለገብ ትግሉ ተጀምሯል። ይህ አመት የትግል አመት ነዉ፤ ይህ አመት የመስዋዕትነት አመት ነዉ፤ ይህ አመት ድል የምናሸትበት አመት ነዉ። ይህ ትግል የገበሬዉን፤ የሠራተኛዉን፤ የወጣቱን፤ የሴቶች እህቶቻችንና የመከላከያ ሠራዊቱን የቀን ከቀን ተሳትፎና መስዋዕትነት ይጠይቃል። እኔም የትግሉን ወደ አዲስና ወሳኝ ምዕራፍ መድረስ እያበሰርኩ ኑና ለክብራችንና ለነጻነታችን እንታገል የሚል የትግል ጥሪ ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አስተላልፋለሁ።
የጀመርነዉን ትግል በድል እንደምንወጣዉ ጥርጥር የለኝም !!!!
መልካም አዲስ አመት -
ደህና እደሩ

tirsdag 9. september 2014

በብሶት የታፈነው ህዝብ አመፅ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት ወያኔ አድሮበታል።

በሳሞራ የኑስ እና በጌታቸው አሰፋ የሚመራ ልዩ የኮማንዶ እና የደህንነት ሃይል አዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋን መቆጣጠር የሚችልበትን ስልት እየነደፈ ነው።
- በሳሞራ የኑስ የሚመራው የኮማንዶ ጦር ህገመንግስታዊ ጥያቄ ማንሳቱ ታማኝነቱ ጥርጣሪ ውስጥ ገብቷል
- መጪው ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ሃይሎች ገነው ይወጣሉ።
- ዲያስፖራው ከምንም ጊዜ በበለጠ ለወያኔ የጎን ውጋትና ራስ ምታት ሆኗል።
- ተቃዋሚ ሃይሎች በአሁን ወቅት ከባድ ጥንካሬ እና የትግል ስልት ሊኖራቸው ይገባል።ጊዜው ነው።
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ በብሶት የታፈነው ኢትዮጵያዊ በቀጣዮቹ ጊዜያት ከፍተኛ አመጽ ያስነሳል በሚል ስጋት ያደረበት እና አመፁ ከመንግስት ሃይሎች ቁጥትር ውጪ ይሆናል በሚል ከፍተኛ ውጥረት በስጋት የተደባለቀበት የወያኒው ጁንታ በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ስብስባ የተቀመጠ ሲሆን ካለፉት ሳምንታት ተከታታይ ስብሰባዎች በተገኙ የውይይት ፍሬ ሃሳቦች መሰረት በሳሞራ የኑስ እና በጌታቸው አሰፋ የሚመራ ልዩ የኮማንዶ እና የደህንነት ሃይል አዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋን መቆጣጠር የሚችልበትን ስልት እየነደፈ ነው።
በአዲስ አበባ የከፍተኛ ለሕወሓት ባለስልጣናት ቅርብ የሆኑት ምንጮች እንደተናገሩት የሚነደፈው ስልት የሕወሓት ባለስልጣናት እምነት ያልጣሉባቸውን የፖሊስ እና ወታደራዊ ሃይሎችን ጨምሮ ህዝቡን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኒታ ልላ ያተኮረ ሲሆን የፖሊስ እና ወታደሩ ክፍል በባለስልጣናት ላይ እርምጃ ይወስዳል በሚል ከፍተኛ ስጋትም እንዳደረባቸው ታውቋል ። የትግራይ ተወላጆች የሆኑትም ፊታቸውን እንዳዞሩባቸው የጠቆሙት ምንጮቹ በከፍተኛ ገንዘብ ከደቡብ ሱዳን ምስራቃዊ ክፍል የሚገኙ እና በስደተኝነት በኢትዮጵያ የኖሩ አማርኛ ቋንቋን የሚናገሩና የሚሞክሩ እንዲሁም ከኑባ ደማዚን ቅጥረኞችን በመግዛት ከቢንሻንጉል ጉምዝ በማምጣት እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ የቀድሞ ታጋዮችን በፖሊስ መልክ በመመልመል በጥሩ ክፍያ በአዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋ ላይ ለማስፈር መታቀዱን ተጠቁሟል። በተለይ በአዲስ አበባ እና በባህር ዳር ይመደባሉ የተባሉ እናበተለያየ ጊዜ በሳሞራ የኑስ የተመረቁ እና በስሩ የሚታዘዙ ኮማንዶዎች እንዲዘጋጁ የተነገራቸው ቢሆንም ባለፈው ሳምንት በነበርቸው ስብሰባ ላይ ህገመንግስታዊ ጥያቂዎችን እንዳነሱ ከታወቀ በኋላ ታማኝነቱ ጥርጣሬ ውስጥ በመግባቱ የወያኒ ስጋቶች ሰፍተው እና ተወጥረው መታየታቸውን ምንጮቹ ተናግረዋል።
የሕዝብ አመጽ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ይሆናል የሚሉት ባለስልጣናት ወታደሩ ክፍል እና የፖሊስ ሰርዊቱ ስለ ተቃዋሚዎች በጎ አመለካከት እንዳይኖረው ከፍተኛ ፕሮፓጋንዳ በየ ክፍሉ እየረጩ ሲሆን የፖለኢስ እና የጦር ሰራዊቱ ግን ጥያቂዎችን ከማንሳቱም በላይ ከካድሬዎች ጋር ፊት ለፊት እስከመሟገት መድረሱ ከቀረበልቸው ሪፖርት የተረዱት ወያኔዎች እንዲሁን ይህን ሰሞን በተለያየ መልኩ አብዮታዊ ዲሞክራሲ በልማት ስም ሽፋን በማድረግ በስልተና መልክ ሲሰጡ የገጠማችው ተቃውሞ ካድሬዎች ፖሊሰና ሰርዊቱ ሕገመንግስታዊ ጥያቄ እንዲያነሳ ማድረጉን የሚያስገነዝብ ሪፖርት በስፋት እንደቀረበ እና ይህንን ሪፖርት ተገትሎ የህዝብ ብሶት ይፈነዳል የሚል ስጋት ወያኒን እያሯሯጠው እንደሆነ ታውቋል።
ምንጮቹ አያይዘውም መጪው ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ሃይሎች ገነው ይወጣሉ። የሚልው የወያኒ ዋና የስብሰባ ነጥብ ገነው እንዳይወጡ በተለይይ የማምከን ስራ ለመጠቀም ቢያስብም ካሁን በፊት የተጠቀመብት ስልት እንዳላዋጣው እና ተቃዋሚዎች ገነው እንዳይወጡ የሚያደርግ የመጨረሻ እርምጃ ለመውስድ የሚያስችል ጥናት በአቶ በርክት ስምኦን በኩል በአስቸኳያ እንዲጠና ሲል ዲያስፖራው ከምንም ጊዜ በበለጠ ለወያኔ የጎን ውጋትና ራስ ምታት እንደሆነና የሀገር ውስጥ ተቃዋሚዎችን በማደረጀት ረገድ ትልቁን ሚና እየትጫወተ እንደሆነ መወሳቱን እና ይህንን ወያኔ መቆጣጠር እንዳቃተው እንደቀጠለ እንዳለ ተነግሯል። ምንጮቹ አያይዘውም ተቃዋሚ ሃይሎች በአሁን ወቅት ከባድ ጥንካሬ እና የትግል ስልት ሊኖራቸው ይገባል ፤ጊዜው ነው። ሲሉ መረጃውን አድርሰውናል።
በሃገር ውስጥ እና በውጪው ህገር የምንገኝ ተቃዋሚዎች ወያኒ በገባበት ስጋት እና ውጥረት ውስጥ ራሱን በራሱ እንዲቀብር ና በኢትዮጵያ ለአንዲና ለመጨረሻ ጊዜ አምባገነንነት እንዲያከትም የዜግነት ድርሻችንን በጋራ የምንወጣብት ጊዜ አሁን በመሆኑ በጋራ ልዩነቶችን በማቻቻል አንዱ አንዱን ሳይወንጅል እና ሳይፈርጅ በተባበረ ክንድ በተገኘው የትግል ስልት ልይ ሁሉ በተገኘው ድርጅት ጋር ሁሉ በመሳተፍ ለነጻነትችን የምንችለውን አስታውጾ ሁሉ እንድናደርግ ይጠበቅብናል። ነጻነት በእጃችን ነው !!

fredag 5. september 2014

በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ካድሬ ለማድረግ የተጠራው ስልጠና በማስፈራራት ተጠናቀቀ

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦
በአፋር ክልል በረእሰ መዲናው በሰመራ የሚገኘው ብቸኛው ዩኒቨርሲቲ ለ10 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የተማሪዎች ሰልጠና ባለፈው ሰኞ ተጠናቀቋል። በስልጠናው የክልሉ የፓለቲካ መሪዎች የተገኙ ሲሆን በአጣቃላይ ሰለ መጭው ምርጫ ቅስቀሳ እንደነበረ ምንጮችን ገልፆል።
afar univercity
እንደ ምንጮቻችን ዘገባ ከሆነ ለመጪውው ምርጫ ኢህአዴግን ምረጡ ካልመረጣቹሁ ግን ስራ አታገኙም በሚል ብዙ ማሰፈራራት የበዛበት ስልጠና እንደነበረ ታውቋል፡
በዚህ አመት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ ተማሪዎች በሰልጠናው የተገኙ ሲሆን በተማሪዎች በኩል ለሚነሱ ወቅተዊ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ማስፈራራትና ማስጠንቀቅ እንደነበረ ታይቷል።
በመጪው ምርጫ ኢህአዴግ እና የክልሉ ፓርቲ አብዴፓ በዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ላይ ያላቸው ድፍራቻ በግልፅ በታየበት በዚህ ስልጠና በክልሉ በግልፅ ስለሚታዩ ችግሮች ላይ የሚናገሩ ተማሪዎች ስማቸው እየተመዘገበ እንደነበረ የአይን እማኞች ገልጸዋል።
በዘንድሮው ምርጫ በመላው ኢትዮጵያ ሊነሳ ስለሚችለው ሁከት ተማሪዎችን ከወዲሁ የማስጠንቀቅ ስልጣና ይመስላል ሲሉ አሰተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።
በኢትዮጵያ ከሚገኙ 9 ክልሎች እስከ አሁን ብዙዎቹም የሚገባቸውን ያህል ባይሆኑም በትምህርት አመስፋፋት ኋላ በመቅረት አፋር ክልል መሪነቱን ይይዛል።

torsdag 4. september 2014

በቂ የገንዘብ ድጋፍ ሲገኝ መንግስት በ1997 ጉዳት ላደረሰባቸው ወገኖች ካሳ እንዲከፍል የሚጠይቀው ክስ እንደሚከፈት ስዊድናዊው የህግ ባለሙያ አስታወቁ

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ1997 ምርጫ ወቅት ለ200 ሰዎች ሞት እና በመቶዎች ለሚቀጠሩት ቁስለኞች ተጠያቂ በሆኑ 13
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ወታደራዊ  አዛዦች ላይ ለፖሊስ የክስ አቤቱታ አስገቡት በስዊድን ታዋቂ የሆኑት ጠበቃ ስቴላ ጋርደ ከኢሳት ጋር
ባደረጉት ቃለምልልስ፣ በቅርቡ ለፖሊስ ከገባው አቤቱታ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በግፍ ለተገደሉት፣ ለቆሰሉት ፣ ለታሰሩት፣ ከስራ ለተፈናቀሉት
አስፈላጊውን ካሳ እንዲከፍል ለማስገደድ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አብዛኛውን የምርመራ ስራ የሚሰራውና ወጪውን የሚሸፍነው የስዊድን ፖሊስ ቢሆንም፣ ምስክሮችን ለማስመጣትና ተጨማሪ ሰነዶችን ለማሰባሰብ ገንዘብ
እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
ገንዘብ የሚያስፈልገው ክሱን ለሚመሰርቱት የህግ ባለሙያዎች አይደለም የሚሉት ስቴላ፣ በክርከሩ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ቢያሸንፍ፣ መንግስት ለሚያቆመው
ጠበቃ ወጪ መከፈል ስላለበትና ወጪውን የሚሸፍነውም የተረታው አካል በመሆኑ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በክሱ ከተረታ ግን በውጭ ያለው ሃብቱ
ታግዶ ለተጎጂዎች እንዲሰጠጥ ይደረጋል ብለዋል።
በ13 የመንግስት ባለስልጣናት ላይ የክስ አቤቱታ ቢቀርብም በመንግስት ላይ እስካሁን አልቀረበም ያሉት ስቴላ፣ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን መዋጪ ማድረግ
ከቻሉና በቂ ገንዘብ እንዳለ ሲታወቅ የካሳ መጠየቂያ ክሱ ወዲያው ይከፈታል ብለዋል። ማንኛውም ገንዘብ አለማቀፍ ደረጃ ባላቸው የሂሳብ ሰራተኞች እንደሚታይና
የተዋጣው ገንዘብ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ሰሞኑን ለፖሊስ የቀረበውን አቤቱታ በተመለከተ ጥያቄ የቀረበላቸው ስቴላ፣ ፖሊስ ማመልከቻውን ተቀብሎ ምርመራ መጀመሩንና በሁለት ወይም ሶስት ሳምንታት
ውስጥ ለስዊድን አለማቀፍ ወንጀል  አቃቢህግ እንደሚያስተላልፍ ተናግረዋል። አቃቢ ህግ የቀረቡትን መረጃዎች አይቶ ክሱን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ ወይም
ላለመውሰድ እንደሚወስን የገለጹት ስቴላ፣ የቀረቡት ማስረጃዎች ክሱ በአጭር ይቋጫል ብለው ለመናገር እንደማያስድፈራቸው ገልጸዋል።
ከአለፉት አስር አመታት ወዲህ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የጦር ወንጀሎች በየትኛውም አገር መታየት መጀመራቸው ክሱን ለመመስረት እንዳነሳሳቸው ጠበቃው
ገልጸዋል።
አቃቢ ህግ ክስ ለመመስረት ከወሰነ ስዊድን ውስጥ ያሉ ተጠያቂዎች በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ፣ ሌሎች ከስዊድን ውጭ የሚኖሩ ባለስልጣናት ደግሞ በኢንተርፖል
በኩል ስማቸው ተላልፎ ተይዘው ክሳቸውን እንዲከታተሉ እንደሚደረግ አክለው ገልጸዋል።
ከጠበቃ ስቴላ ጋርደ ጋር ያደረግነውን ቃለመጠይቅ በነገው ዝግጅት ይዘን እንቀርባለን።

ሕወሃት/ኢሓዴግ ምን ያህል እንዳከረረ (ክፍል 2) – ግርማ ካሳ

አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች አመራር አባላት ናቸው። አብርሃ ደስታ ከአረና፣ ዳንኤል ሺበሺና ሃብታሙ አያሌው ከአንድነት፣ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ። ሐምሌ 1 ቀን 2006 ሽብርተኞች ናችሁ ተብለው ተያዙ። ጠበቃዎቻቸው በሌሉበት በድብቅ ፍርድ ቤት ቀረቡ ተባለ። ፖሊስ ዜጎችን ከመያዙ በፊት በእጁ መረጃ ሊኖረው ሲገባ፣ መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሎ ለ28 ቀናት ቀጠሮ ይጠይቃል። ፍርድ ቤቱ፣ ያለምንም ማቅማማት፣ ምን መረጃ በሌለበት ሁኔታ፣ የታሳሪዎችን የዋስትና መብት ከልክሎ 28 ቀናትም እንዲታሰሩ ያዛል።
ከ28 ቀናት በኋላ ሃብታሙ፣ ዳንኤል እና የሺዋስ ነሐሴ 27 ቀን እንደገና ፍርድ ቤት ቀረቡ። አሁንም ፖሊስ ማስረጃ ሳያቀርብ ለ28 ቀን ሁለተኛ ቀጠሮ ጠየቀ። ፍርድ ቤቱ አሁንም፣ ምንም መረጃ ሳይመለከት፣ ፖሊስ ስለጠየቀ ብቻ፣ ዜጎች በወህኒ እንዲቆዩ አዘዘ። አምሣ ስድስት ቀናት መረጃ ሳይቀርብ ዜጎች ሕግ ያስከብራል በሚባለው አካል የሰብአዊ መብታቸው ተረገጠ። እንደገና ለመስከረም 22 ቀን ተቀጠሩ። ነሐሴ 29 ቀን ደግሞ አብርሃ ደስታ ፍርድ ቤት ሲቀርብ የተለየ ነገር አልነበረም። «ተጨማሪ ሰነድ ለማሰባሰብና ምስክሮች ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልገኛል» ብሎ ፖሊስ በመጠየቁ ተጨማሪ 27 ቀን ይሰጠዋል።
እነዚህ የታሰሩ ወጣት ፖለቲከኞች የሰሩት አንዲት ወንጀል የለም። ወንጀላቸው ለፍትህ፣ ለሰላም፣ ለዲሞክራሲ መቆማቸው ነዉ። ወንጀላቸው አገራችውን መዉደዳቸው ነው። የሕወሃት/ኢሕአዴግ አገዛዝ ግን፣ ሕግን እንደ በተር በመጥቀም፣ ጠንካራ የሚባሉ፣ ተሰሚነት ያላቸውን ወጣት የፖለቲካ አመራሮች በማሰር፣ ሆን ብሎ የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ ለማሽመድመድ እየሞከረ እንደሆነ ግን ግልጽ ነው።
ከዘጠና ሰባት በኋላ በተፈጠረው ሁኔታ «ቅንጅት ሞቷል፤ የተቃዉሞ እንቅስቃሴውም አልቆለታል» በሚል ሕወሃት/ኢሕአዴጎች ዳንኪራ ሲመቱ እንደነበረ ይታወቃል። ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የተበታተነዉን አሰባስባ አንድነት በሚል ስም ጠንካራ ፓርቲ እንዲወጣ አደረገች። የአገዛዙ ባለስልጣናት 50 ሰው አይገኝም ያሉት፣ በሜክሲኮ አደባባይ መብራት ኃይል አዳራሽ ያኔ በተደረገው፣ የመጀመሪያው የአንድነት ሕዝባዊ ስብሰባ፣ ከ5 ሺህ ሰው በላይ በመግባቱ አዳራሹ ሞላ። የአዳራሹ በር ተዘግቶ ብዙ ህዝብ እንዲመለስ ተደረገ። በአራት ኪሎ ያሉ ባለስልጣናት ደነገጡ። ሰበብ ፈልገው ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን አሰሯት። ኢንጂነር ግዛቸው ሃላፊነቱን ያዙ። ነገር ግን የፓርቲው እንቅስቃሴ ተዳከመ። አንድነት ተከፋፈለ። በድጋሚ በሕወሃት/ኢሕአዴጎች ዘንድ ፌሽታ ሆነ።
አንድነት ዉስጥ እንደ አንድዋለም አራጌ ያሉ ወጣት አመራሮች መጡ። መጠነ ሰፊ ድርጅታዊ ሥራ መስራት ጀመሩ። ትንሽም ብትሆን አንድነት በአገሪቷ ሁሉ ድርጅታዊ መዋቅሩን መዘርጋት ጀመረ። የአንድነት ጥንካሬ ያሳሰበው ሕወሃት/ኢሕአዴግ እንደገና በትሩን አነሳ። አንድዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን የመሳሰሉ ጠንካራ አመራሮች ታሰሩ።
ብዙም አልቆየም ተወዳጁ እና ተስፍ ሰጪው የሚሊየነሞች ንቅናቄ ተጀመረ። በሌላ በኩል ከመኢአድ ጋር አንድነት የሚያደርገው የውህደት እንቅስቃሴ ትልቅ መነቃቃትን ፈጠረ። የአንድነት ፓርቲ ገዢዎች ከጠበቁት እና ከገመቱት በላይ ገፍቶ ስለሄደባቸው በድጋሚ በትራቸውን አነሱ። በሚሊዮኖች ንቅናቄና በመኢአድ አንድነት ዉህደት ዙሪያ፣ ትልቅ ሚና የነበረው፣ የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ፖለቲከኛው ሃብታሙ አያሌውን አሰሩት። በተለይም በደቡብ ክልል ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ ሲሰራ የነበረዉን የፓርትቲው ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዳንኤል ሺበሺንም እንደዚሁ። የአንድነት መሪ የሆኑት ኢንጂነር ግዛቸው ፣ ሃብታሙ ከታሰረ በኋላ የሚሊየነኖምችን ንቅናቄ ማስኬድ አልቻሉም። እንቅስቃሴው ባለበት ቆመ። ወደፊትም ቆሞ የሚቀር ይመስላል፣ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ግፊት አድርገው ፓርቲው ከቢሮ ወደ ሜዳ እንዲወጣ ካላደረጉት በቀር።
በአብዛኛዉ የአገዛዙን በትር የቀመሰው የአንድነት ፓርቲ ቢሆንም፣ ሰማያዊ፣ አረና እንዲሁም ሌሎችም አላመለጡም። የሰማያዊ እና የአንድነት አብሮ መስራት ፣ ብሎም መዋሃድ ፣ የአንድነት እና የመኢአድ መዋሃድ የአገዛዙ ራስ ምታቶች ነበሩ። በተቻለ መጠን ሰማያዊን እና አንድነትን ማራራቅ፣ አንድነት እና መኢአድ እንዳይዋሃዱ ማድረጉን ትልቁ ግባቸው አድርገው ነበር ሲሰሩ የነበሩት። በመሆኑም የሚቆጣጠሩትን ምርጫ ቦርድ ተጠቅመው፣ የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደትን ለጊዜው አደናቀፉ። በሰማያዊና በአንድነት መካከል መቀራረብ እንዲኖር ይተጋ የነበረዉን የሰማያዊ ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ የሺዋስ አሰፋንም ወደ ወህኒ ወሰዱት።
በሰሜን የሕወሃት እምብርት በሆነችዋ ትግራይ፣ የፍትህና የዲሞክራሲ ድምጽ ሆኖ ሲጽፍ የነበረው፣ የአረና አመራር አባል አብርሃ ደስታ፣ ለሕወሃቶች ትልቅ ራስ ምታት ነበር የሆነባቸው። እነርሱ ጠመንጃ ይዘዋል። እርሱ ግን ብእር ብቻ ነበረች በእጁ። በትግራይ ዉስጥ ትልቅ ንቅናቄ መፈጠሩን፣ የትግራይ ሕዝብ ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር አብሮ ለትግል እጅ ለእጅ መያያዙ አስደነገጣቸው። ሕወሃቶች ሊኖሩ የሚችሉት ህዝቡን ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ እያሉ ሲከፋፍሉት ብቻ ስልሆነ፣ ኢትዮጵያዉያንንን የማሰባሰብ ፖለቲካን ይጸየፉታል። በተለይም በአብርሃ ደስታ ግፊት መቀሌ ሰላማዊ ሰልፍ ሲጠራ፣ ሰልፉ እንዳይደረግ መከልከል ሳይበቃቸው፣ የሰልፍ ጥያቄ እንደገና እንዳይነሳ በሚል ነው መሰለኝ አብርሐ ደስታን ከነሃብታሙ ጋር ወደ ማእከላዊ አስገቡት።
እንግዲህ ከላይ የጠቀስኳቸው በሙሉ የሚያሳዩት ሕወሃት/ኢሕአዴጎች ምን ያህል የተጨበጠ ሥራ የሚሰሩ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ማየት እንደማይፈልጉ ነው። እነርሱ የሚፈልጉት ዝም ብሎ መግለጫ የሚያወጡ፣ ዝም ብለው የሚያወሩ፣ ዝም ብለው ስብሰባ ማድረግ የሚቀናቸው፣ ከቢሯቸው የማይወጡ፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የማያደርጉ፣ ትግሉን ወደ ሜዳ የማይወስዱ መሪዎችን እና ድርጅቶችን ነው። እንደነዚህ አይነት ድርጅቶች እየጠቀሱ የዉሸት መድበለ ፓርቲ እንዳለ ለማሳየት የሚጠቀሙባቸው ድርጅቶች ናቸው።
አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ «የዲሞክራሲ ስርዓት መገንባት ለኛ አማራጭ ሳይሆን ሕልዉናችን ነው» ሲሉ ብዙ ጊዜ ሰምቻቸዋለሁ። ዶር ቴዎድሮስም አዳኖምም አንድ ወቅት ከጆን ኬሪ ጎን ለጎን ቆመው፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዲሞክራሲ እንደሚያብብ ነበር የነገሩን። ነገር ግን እያየን ያለው፣ ከመለስ ዘመን በባሰ ሁኔታ ሕወሃት/ኢሕአዴግ እንዳከረረ ነው። አቶ ኃይለማሪያም፣ መለስን አውት ሻይን ለማድረግ ነው መሰለኝ፣ ብዙዎችን በማሰር፣ በማስገደል፣ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን በመጨፍለቅ በጣም እየተጉ ናቸው።
አንድ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች የዘነጉት ነገር ቢኖር ግን ትግሉ፣ የፖለቲክ ድርጅት መሪዎች ብቻ ሳይሆን የሕዝብ መሆኑን ነው። የሕዝብን ኃይል ደግሞ አፍነው ሊቆዩ አይችሉም። ሕዝብ ምንጊዜም አሸናፊ ነው።