fredag 15. mai 2015

አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን። የጋራ መግለጫ

stamps Joint press release
አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን።
የአንድነት፣ የመከባበር፣ የመቻቻል እና የነፃነት ምሳሌ የሆነችው አገራችን እኩይ አላማቸውን ለማሳካትና የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም በሚንከላወሱት የወያኔ ቡደን አገራችንና ሕዝባችን ከምንግዜውም በከፋ ደረጃ ላይ አድርሰዋታል።
ወጣቱ በአገሩ ላይ ተምሮና ሰርቶ የመኖር እድሉ ለወያኔው አገዛዝ ማደር አልያም አገሩን ጥሎ መሰደደ በሆነበት ሁኔታ ውስጥ አገሩን ጥሎ የሚሰደደው ዜጋ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለመሰደድ በሚያደርገው ጉዞ ምን ያህሉ በበርሃ እንደሚቀርና የአሳ እራት እንደሆነ የመገናኛ ብዙሃን በሰፊው ሲዘግቡት ቆይተዋል።
በተለያየ አገር በስደት ከሚፈልጉት አገር የደረሱትና የእለት ጉርሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለማገዝ ደፋ ቀና በሚሉበት ሂደት ውስጥ በደቡብ አፍሪካ በቁማቸው በአሳት መቃጠል፣ በሊቢያ አይናቸው እያየ መታረድና በጥይት መደብደብ ሆኗል እጣ ፋንታቸው።
እናም አገርና ሕዝብ በእንደዚህ አይነት አስከፊ ሂደት መቀጠል የለበትም የወያኔም የግፍ አገዛዝ ሊበቀው ይገባል በሚል ቀደም ብለን ይህን በታኝ ስርዓት በትጥቅ ትግል እየተፋለምን ያለን ደርጅቶች እኛ አንድ ሆነን ሕዝቡን አንድ በማደረግ አገራቸንና ሕዝባችንን ነፃ ማውጣት የሚገባን ወቅት አሁን ነው በሚል ስርዓቱን ለማስወገድ በሚደረገው የትግል ሂደት በትብብር መስራት አለብን በሚል ውይይት ጀምረናል።
ወደፊት በሚኖረው የትግል ሂደት በትብብር፣ በጥምረት ብሎም በውህደት ለመስራት በውይይት ላይ የምንገኘው ድርጅቶች፡-
1. የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
2. የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
3. የቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
4. የአማራ ዴሞክራሲ ሃይል ንቅናቄ
5. አረበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ
ስንሆን ከሁሉም አስቀድመን አገራችንና ሕዝባችን ማዳን ግባችን አድርገን እንስራ በሚል መርህ በማንኛውም መንገድ አብረን መስራት አለብን ወደ ፊት ምንም አይነት ልዩነት ይኖረናል ብለን ባናምንም በሂደት ወደ አንድ የምንመጣበትን ሁኔታ እያመቻቸን አሁን ግን አገርና ሕዝብን የማዳኑን ስራ እንጀምር በሚል ውይይት እያደረግን መሆናችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መግለፅ እንወዳለን።
አምባገነኑም የወያኔ ቡድን እንዳለፉት ምርጫዎች ሁሉ በቅርቡ የሚደረገውን የይስሙላ ምርጫ ለማድረግ ደፋ ቀና እያለ ሲሆን በተለያየ አገራት በእናትህ፣ በአባትህ፣ በወንድምህ፣ በእህትህ ላይ ላይ እየደረሰ ላለው ዘግናኝ ግፍ እንኳን ወቅቱን ጠብቆ ተቃውሞውን ያልገለፀ ኢትዮጵያዊ ባህሪ የለሌው እኩይ ሥርዓት በመቃወም ረገድ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገህ ቢሆንም በተደራጀ ሁኔታ እየታገልን ከምንገኘው ተቃዋሚ ድርጅቶች ጎን በመሰለለፍ አስፈላጊውን አስተዋጽዖ እንድታደርግ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
አንድነት ሃይል ነው!!!
30/08/2007 ዓ.ም

አይሲስን ስንቃወም ህወሓትን አለመርሳት!

May 13, 2015
በአይሲስ በግፍ በታረዱብን ወገኖቻችን የተሰማን ሀዘንና ቁጭት ከፍተኛ ቢሆንም እንኳን ከአዕምሮዓችን መውጣት የሌለበት ሀቅ አለ። ይህ ሀቅ “ያስጠቃን፣ ያሳረደን ወያኔ ነው” ከሚለውም ያለፈ ነው። መረሳት የሌለበት ሀቅ፣ ከአይሲስ የከፋ ጨካኝ በአገራችን የመንግሥት ሥልጣን የተቆጣጠረ መሆኑ ነው።
የህወሓት ፋሽስት ጦር በበደኖ፣ በአዋሳ፣ በሀረር፣ በጋምቤላ፣ በጎንደር፣ በኦጋዴን፣ በአዲስ አበባ፣ በሸካና መዠንገር፤ እንዲሁም በሚታወቁም በማይታወቁም የማሰቃያ እስር ቤቶች አይሲስ እየፈፀመ ካለው የባሱ ወንጀሎች በወገኖቻችን ላይ ፈጽሟል፤ አሁንም እየፈፀመ ነው። ባሳለፍነው ሣምንት እንኳን በሁመራ ወገኖቻችን የራሳቸውን መቀበሪያ ጉድጓድ ቆፍረው በጅምላ ተገድለዋል። በአይሲስና በህወሓት መካከል ያለው ልዩነት አይሲስ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሩን በቪዲዮ እየቀረፀ ለዓለም ሲበትን ህወሓት ግን እነዚሁኑ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሮችን እየፈፀመ መረጃዎች አፍኖ መያዙ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ግን ህወሓት ሰዎችን ከነሕይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ የቀበረ አረመኔ፣ እኩይ ድርጅት ነው።
ስለሆነም ለዓለም ሰላም ስጋት የሆነውን አይሲስን ስንቃወም የራሳችንን አይሲስ – ህወሓትን – አለመርሳት እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት፣ የአይሲስን እኩይ ተግባራት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር እና ከዲሞክራሲያዊያዊ ፓለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ጋር ለማገናኘት እያደረገ ያለው ጥረት ምን ያህል አደገኛ ተግባር እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል። ዓይን አውጣ ሌባ ንፁሁን ሰው “ሌባ” እንደሚለው ሁሉ የኛው አይሲስ ራሱን ንፁህ አስመስሎ ሌሎችን “አይሲስ” ማለቱ ሊነቃበት ይገባል።
ሌላው ተያያዥ ጉዳይ ደግሞ ስለስደተኝነት የሚሰጠው ገለፃ ነው። ህወሓት ለስደተኝነት ምክንያቱ ደላሎች እንደሆኑ ይናገራል። ይህ የጉዳዩን ግንድ ትቶ ቅርንጫፎች ላይ ማትኮር ነው። ህገወጥ ደላሎች ራሳቸው ሊኖሩ የቻሉት ገንዘብ ከፍለውና የሕይወት ሪስክ ወስደው ለመሰደድ የሚፈልጉ ዜጎች በመኖራቸው ነው። ችግሩን በቅንነት ለመመርመር የሚፈልግ “ይህን ያህል ሰው የሕይወት ሪስክ እየወሰደ ከአገር ለመሰደድ ምን አነሳሳው?” ብሎ መጠየቅ እና ምላሽ ማግኘት ይኖርበታል። በሀገር ውስጥ በነፃነት ተረጋግቶ መኖር፣ ሠርቶ የማደግ ተስፋ ቢኖር ኖሮ ይኸን ያህል ሰው የአደጋውን ከፍተኛነት እያየ ለመሰደድ ይነሳሳ ነበርን? ኢትዮጵያዊው ከስደት ሊያገኝ የሚሻው ምንድነው? እንደ ወያኔ ካድሬዎች ገለፃ ከሆነ ከስደት ሊያገኝ የሚችለው አገሩ ውስጥ እያለለት ነው ኢትዮጵያዊ የሚሰደደው። ይህ ምን ዓይነት አመክኖ ነው? ከዚህ የባሰው ደግሞ ስደትንም የእድገት ውጤት አድርጎ የማቅረብ በሽታ ነው። ይህ እውነት ከሆነ፤ ህወሓት ለኢትዮጵያ አመጣሁላት የሚለው እድገት ውጤት ረሀብ፣ ስደት፣ መርዶ፣ እስር፣ ስቃይ፣ ሞት ከሆነ እንዴት “እድገት” ብለን እንጠራዋለን። ለስደተኝነት መብዛት ህገወጥ ደላሎችን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ፤ “እኔ ከደሙ ንፁህ ነኝ” የማለት ያህል ነው። በህጋዊዎቹም በህገወጦቹም ደላሎች ውስጥ የወያኔ ሰዎች በቀጥታም በተዘዋዋሪም እንዳሉበት መረጃዎች ያመለክታሉ። ገንዘብ ባላበት ሁሉ የወያኔ እጅ መኖሩ ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። የሰዎች ዝውውር የህወሓት አንዱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ መሆኑ የማይታበል፤ በቀላሉ ማረጋገጥ የሚቻል ሀቅ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በዓለም አቀፉ አይሲስ አረመኔያዊ ተግባሮች በደረሰብን የመጠቃት ስሜት ተውጠን የራሳችንን አይሲስ – አረመኔውን ህወሓት – እንዳንረሳ ያሳስባል። መቆሚያው ለማይታየው የዜጎቻችን መሰደድ መንስኤዎች የነፃነት እጦት እና የኑሮ እድሎች መጥበብ መሆናቸው እንዳንዘነጋ ይጠይቃል። ንቅናቂያችን እነዚህ ተያያዥ ችግሮች ሁሉ የሚቃለሉት ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑባት ኢትዮጵያን ስንመሰረት ብቻ ነው ይላል። ለዚህም ደግሞ ሁላችንም በያለንበት የበኩላችንን ተሳትፎ ማድረግ ይገባናል። ሁለገብ ትግል ማለት፤ እያንዳንዱ ከሚመስለው ጋር እየተደራጀ በያለበት ወያኔ ማስጨነቅ፣ ማዋከብና ማዳከም፤ በመጨረሻም በጋራ ትግል ማስወገድ ማለት እንደሆነ ልብ እንበል። በሁለገብ ትግል ለውጥ የሚመጣው ሁሉም እንደ አቅሙ
በሚያደርገው ተሳትፎ በመሆኑ፣ የሚቻለንን በማድረግ የለውጥ ጠባቂ ሳንሆን፣ የለውጥ አምጭ አካል እንሁን ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
Source www.patriotg7.org

tirsdag 5. mai 2015

Election, Ethiopian Style

Since the last election, the ruling party has exerted more control and increased its repression of basic liberties.


There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent, writes Horne [Al Jazeera]
There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent, writes Horne [Al Jazeera]
This is what an election campaign looks like in Ethiopia, where the ruling coalition took 99.6 percent of parliamentary seats in the last national elections, in 2010.
Jirata, who asked that his real name not be used, is a 19-year-old student who was campaigning for a legally registered opposition party recently, when security officials arrested him.
They told him that he was working for a "terrorist group" that sought to forcibly bring down the government. He was badly beaten over the course of three nights and released on the condition that he end his involvement in politics. He is still limping from his injuries, and he told me he no longer has any interest in getting involved in politics. He says he will vote for the government party "because life is easier that way".
Ethiopia: Journalism under anti-terrorism law
Jirata was working for an Oromo party, representing an ethnic group long targeted by the government. But as Ethiopians go to the polls in late May, the prospects for opposition parties to fully and fairly campaign are grim.
Since the last election, the ruling party has only exerted more control and increased its widespread repression of basic liberties, including the rights to free expression, assembly, and association.
The courts provide no justice in cases of political importance. While election day is unpredictable, it's clear that the avenues by which opposition parties can fully function and citizens can engage on political issues are largely closed.
While there are 75 registered opposition groups, several of the largest parties have talked of boycotting the elections because of flawed electoral processes. Challenges with registering candidates, acquiring the funds they are legally entitled to, mobilising their supporters, and keeping their members out of prison have taken their toll.
In short, there is limited space for government critics to play a peaceful and constructive role.

Suppression of non-governmental voices
The Ethiopian media provides little coverage of relevant political issues ahead of the election since what vestiges of independent media existed have largely been eliminated since 2010.
Reporters critical of the government are regularly harassed, threatened and detained. In 2014 alone, over 30 journalists fled Ethiopia and at least six publications were closed down.
Sources providing information to media and human rights groups are regularly targeted. Many diaspora media websites, while heavily politicised, remain blocked in Ethiopia. Journalists must choose between self-censorship, harassment, imprisonment, and exile.
The situation hasn't been much better for opposition parties that want to organise peaceful protests and rallies ahead of the election. The Semayawi party (Blue Party), for example, is one of the newcomers in Ethiopia's electorallandscape, and since 2013 has tried to hold regular and peaceful issue-based protests.
Protesters and organisers have frequently been arrested and harassed, their equipment has been confiscated, and permits unfairly denied. One of their leaders is on trial on trumped-up terrorism charges.
The lone opposition parliament member is not running this time due to a split in his party, the Union of Democracy and Justice, in which Ethiopia's national electoral board played favourites. The net effect is that the government awarded the party name to an offshoot of the party that is more closely aligned to government policies and interests.
No dissent allowed
There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent or to contribute to the national political dialogue. Dissent of any type, particularly in rural areas, is dealt with harshly. The long-standing 5:1 system of grassroots surveillance - under which one individual is responsible for monitoring the activities of five households - has let local officials clamp down on dissent before it spreads beyond the household level.Telephone surveillance is commonplace, and the ongoing trial of a group of bloggers called Zone 9 has resulted in increased self-censorship online.
In short, there is limited space for government critics to play a peaceful and constructive role. The only international observers to the election will be the African Union. The European Union is not sending observers, noting that Ethiopia has not implemented recommendations by previous election observers. As Human Rights Watch documented after the 2010 elections, those who complain about election irregularities risk arrest and harassment.
"If we have an issue with government where do we go?" an Ethiopian who lives in a rural area recently told me, summing it up: "There is no media that will write our story, there are no more organisations that work on issues that the government does not like, if we take to the streets we are arrested, and if we go to their office to question we are called terrorists. If we go to the courts, there is no independence - we go to jail. There are no large opposition parties to vote for in the election, and even if there were, if we vote for them our lives then become very difficult. So what can we do? The elections are just another sign of our repression."
Source: Al Jazeera

søndag 3. mai 2015

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

fredag 1. mai 2015

የማዕከላዊ እዝ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መምጣቱ ታወቀ

mekononoch serawitየማዕከላዊ እዝ  ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መሄዱ ስላሳሰባቸው የእያንዳንዱን ወታደር ንብረት እየፈተሹ በርካታ ወታደሮችን ማሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ፣በምንጮቻችን መረጃ መሰረት የማዕከላዊ እዝ አመራሮች በየዕለቱ የሚከዳው የሰራዊት ቁጥር ስላሳሰባቸው ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ/ም የእያንዳንዱን ወታደር የግል ንብረት ሲፈትሹ የዋሉ ሲሆን በፍተሻውም ከ180 በላይ የሚሆኑት የሲቪል መታወቂያ ካርድ ያላቸው ወታደሮች መገኘታቸውን አስረድቷል፣
ይህ የተገኘው የሲቪል መታወቂያ ካርድም ከትውልድ ቦታቸው በተለያዩ መንገዶች የተላከላቸው ሲሆን ሲቪል መስለው ስርዓቱን እየጣሉ ለመሸሽ እንዲያግዛቸው የተዘጋጀ መሆኑን የገለፀው መረጃው በዚህ የተነሳም አራት ነባር የሰራዊት አባላቶች ለ3 ወር እስራት ተወስኖባቸው በአዲ ኮኮብ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፣
ምንጭ -ዴምህት

የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴ የሺሻ ማጨሻ ሆነ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ያስገነባው እና ዘመናዊ ተብሎ የሚጠራቅ ቀነኒሳ ሆቴል በሺሻ ማጨስ የተለከፉ ወጣቶች መጠራቀሚያ እና ጥራቱን ያልጠበቀ ስራ በመስራት የሚታወቅ ሆቴል ሆⶈል ። በአዲስ አበባ ከተማ ወጣት ሴቶች ከተለያዩ ጓደኞቻቸው ጋር የሚቀጣጠሩበት ዋነኛ መድረክ የሆነው ሺሻ ወይንም ሁካ ማጨሻ ስፍራዎች ሲሆኑ ፣በአሁን ሰአት ግን ይህ ሆቴል የሆቴሎች አስተዳደር ድርጅት እና የአዲስ አበባ ስራ እና ከተማ ልማት ቢሮ የሰጠውን፡ሕጝ፡ጥሶ የሺሻ ማጨሻ ሱቅ ማድረጉ በጣም አሳፋሪ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል ።
ቀነኒሳ በቀለ ሆቴሉን ካሰራ በሁዋላ የፊት ለፊት ገጹን የስሙን ጽሁፍ በቻይንኛ ማሰራቱ በሃገሩ ቋንቋ እና በማንነቱ የማይኮራ ነው ሲባል የተወቀሰ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ፣በሌላም በኩል ከፍተኛውን ስራ የሰሩት ቻይናዎች ሲሆኖ ጫና አሳድረውበት ነው ሲሉ ገልጸዋል ;በሌላም በኩል በአማካሪው ግፊት ነው የቻይንኛ ቋንቋ የመሰለ ፊደል ሊጠቀም የቻለው ሲሉም 

በተለይም እንደ አትሌት ቀነኒሳ አይነት የስፖርት ቤተሰብ የሆነ ሰው እና በህዝብ ዘንድ በስራው ገናናነትን ያተረፈው ድንቅ አትሌት ወጣቶችን ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠቡ መምከር ሲገባው በእራሱ ባሰራው ህንጻ ላይ ታዳጊ ወጣቶች እንዲበላሹ መጋበዙ አሳፋሪ እና ከእሱ ስራ እና ክብር የማይጠበቅ ነው ሲሉ ወርፈውታል ።
በሌላም በኩል ሆቴሉ የሚያቀርባቸው አግልግሎቶች ውስጥ ማናቸውም ከሁካ ወይንም ሺሻ ጋር የሚቀርቡ መጠጦችም፡ምግቦች ዋጋቸው የናረ ከመሆኑም በላይ መንግስት ያለቀረጥ የሚነግዱትን እንደሚያስር እና እንደሚቀጣ ሁሉ የአትሌት ቀነኒሳ ስራ ከማናቸውም ሆቴሎች ደረጃ በላይ ውድ መሆናቸው በላይም የመንግስት አስተዳደር ዝምታውን መምረጡ ተገቢ አይደለም ሲሉ አክለው ገልጸዋል ።
ሆኖም ግን በዚህ የሺሻ መሸጫ መደብር የሆነው የቀነኒሳ ሆቴል ውስጥ፡ባለ፡ስልጣናት እና የባለስልጣናት ልጆች ጊዜ ማሳለፊያቸው እና መዋያቸውንም ዘጋቢያችን ወይዘሪት ኢትዮጵያ ከስፍራው ገልጻለች ። ማለዳ ታይምስ

torsdag 19. mars 2015

በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግሰለቦች የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ ! ‹‹ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ የህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ›› አብርሃ ደስታ


በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግሰለቦች የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ
‹‹እኔ አሸባሪ አይደለሁም፡፡ ኢህአዴግ አሸባሪ ነው፡፡ ለሽብር ሀሳቡም ፍላጎቱም የለኝም›› ዳንኤል ሺበሺ
‹‹የተባለውን ለነገር አለማድረጌን ከእኔ በላይ የከሰሰኝ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል›› ሀብታሙ አያሌው
‹‹ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ የህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ›› አብርሃ ደስታ
‹‹ይሄ 19ኛ ችሎት የጦር ፍርድ ቤት ችሎት እየመሰለ ነው›› የሺዋስ አሰፋ
‹‹ሃይማኖቱንና ማኅበረሰቡን ከሚፈራ ህዝብ ወጥቼ እንዲህ አይነት ተግባር አልፈጽምም›› ባህሩ ታዬ
————————
ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2007 ዓ.ም፣ በከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙት እና በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ያሉ 10 ሰዎች ቀርበው ነበር፡፡ መዝገቡ ለዛሬ የተቀጠረው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ለመቀበል እና ከ1-5ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተከሳሾች በእስር ቤቱ ደረሰብን ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ላይ አስተያየት ካላቸው ለመቀበል መሆኑን የችሎቱ የግራ ዳኛ ገልጸዋል፡፡
የተከሰሾቹን የጽሑፍ አስተያየት በጠበቃ ተማም አባቡልጉ በኩል ቀርቦ ከመዝገብ ጋር ከተያያዘ በኋላ ተከሳሾቹ በየተራ የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ የግራ ዳኛው በመናገር 1ኛ ተከሳሽን ‹‹በክሱ ላይ እንደቀረበው ወንጀሉን ፈጽመሃል ወይስ አልፈጸምክም?›› ሲሉ ጠየቁት፡፡
ዘላለምም ‹‹አቃቤ ሕግ ባላደረኩት ነገር ህጉን መደገፍ ስለሚሆንብኝ ምንም መልስ አልሰጥም›› ሲል ዳኛው ‹‹በሥነ ሥርዓት ሕጉ ክሱን ክደው ተከራክራል› በሚል መዝግበነዋል›› በማለት መዝገብ ላይ አሰፈሩ፡፡
2ኛ ተከሳሽ አቶ ሃብታሙ አያሌው በበኩሉ ‹‹የተባለውን ለነገር (ሽብር) አለማድረጌን ከእኔ በላይ የከሰሰኝ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል፤ እረዳለሁም፡፡ አቃቤ ሕግ ለምን እንደከሰሰኝም አውቃለሁ፡፡ የቆምኩለትን ሕጋዊ ፓርቲንም አፍርሶታል፡፡›› ብሏል፡፡
3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺም ‹‹ሽብር የሚባለውን ነገር የሰማሁት ከሟቹ ኦሳማ ቢንላዳንና ከዘቶ መለስ ዜናዊ ነው፡፡ አደረክ ለተባልኩት ነገር ሃይማኖቴ፣ ዓላማዬ …አይፈቅድም፡፡ በዚህ ምክንያት ቤቴ እንዲወሰድ ተደርጓል፡፡ እኔ አሸባሪ አይደለሁም፡፡ ኢህአዴግ አሸባሪ ነው፡፡ ለሽብር ሀሳቡም ፍላጎቱም የለኝም፡፡ መንግሥት ፓርቲዬን ለማፍረስ የፈነቀለው …›› ብሎ ሳይጨርስ ፍርድ ቤቱ ንግግሩን እንዲያቋርጥ አስገድዶታል፡፡
4ኛ ተከሰሽ አብርሃ ደስታ መናገር ከመጀመሩ በፊት ‹‹ድርጊቱን መፈጸም አለመፈጸምህን ብቻ ተናገር›› ተብሎ ከችሎቱ ተነግሮት ነበር፡፡ አብርሃም በተረጋጋ መንፈስ ‹‹መልሱ እሱ አይደለም፤ የፈለኩትን እናገራለሁ፡፡ ሀሳቤን ልግለጽ›› ሲል ተናገረ፡፡ ዳኞች ሳይዋጥላቸው እንዲናገር ፈቀዱ፡፡ ‹‹ክሴ ከአሸባሪ ጋር በመገናኘት …የሚል ነው፡፡ አሸባሪ ለሚፈልገው ዓላማ ሰላማዊ ያልሆነ /ሰውን የሚጎዳ ድርጊት የሚያስፈጽም ነው፡፡ ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ ህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ …›› የግራ ዳኛው የአብርሃን ንግግር አቋረጡትና ‹‹ክሱ ላይ ህወሃት/ኢህአዴግ የሚል የለም፡፡ ክሱን መቃወም አለመቃወምህን ብቻ ተናገር›› አሉት፡፡ አብርሃም ‹‹ሕወሃት /ኢህአዴግ፣ ደህንነቱ ማፊያ ነው … ›› ዳኞቹ በድጋሚ አቋረጡት፡፡ አብርሃ ‹‹አልጨረስኩም›› ቢልም ዳኞቹ ከዚህ በላይ ሊሰሙት አልፈቀዱም፡፡
5ኛ ተከሳሽ የሺዋስ አሰፋም ‹‹ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ ነው የምናገረው፣ ስሙኝ›› ሲል ለችሎት ገለጸ፡፡ ዳኞቹ ክሱን መቃወም አለመቃወሙን ብቻ እንዲናገር ገለጹለት፡፡፡ የሺዋስ ‹‹ትንሽ ሁለት ደቂቃ የምትሞላ ንግግር ነች፡፡›› አላቸውና ቀጠለ፡፡ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 75/4 ላይ ልዩ ፍርድ ቤት ስለማቋቋም ይደነግጋል፡፡ ይሄ 19ኛ ችሎት የጦር ፍርድ ቤት ችሎት እየመሰለ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ ዳኞች ነጻ ስለመሆናቸው ይደነግጋል፡፡ የእኔ ችግር ችሎቱ ላይ ነው፡፡…›› ዳኞች የየሺዋስን ንግግር አቋረጡት፡፡ የሺዋስም ‹‹ዛሬ ብቻ ነው የምናገረው›› በማለት እንዲህ አለ፡- ‹‹በሕገ-መንግሥቱ ላይ ዳኞች ነጻ መሆን እንዳለባቸው ቢቀመጥም የመርማሪ እና ዐቃቤ ሕጎችን ሀሳብ ብቻ የሚሰማው፤ እኛን አይሰማ አሻንጉሊት ፍርድ ቤት ነው፡፡…›› የሺዋስም መናገር የቻለው ይሄን ብቻ ነው፤ ዳኞች ድጋሚ አስቁመውታል፡፡
6ኛ ተከሳሽ፣ ዮናታን ደግሞ ‹‹ያለፈቃድ እንድተውን እየተገደድኩ ነው›› ብሏል፡፡ 7ኛ ተከሳሽ (ስሙን የዘነጋሁት) ‹‹የተቀነባበረ ክስ ስለሆነ ምንም ማለት አልችልም፡፡›› ሲል 8ኛ ተከሻሽ ባህሩ ታዬም ‹‹ሃይማኖቱንና ማኅበረሰቡን ከሚፈራ ህዝብ ውስጥ ወጥቼ እንዲህ አይነት ተግባር አልፈጽምም፣ አለፈጸምኩምም፡፡ …ጊዜ እውነቱን ይፈርዳል›› ሲል ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 9ኛ እና 10ኛ ተከሳሾችም ‹‹ድርጊቱን አልፈጸምንም›› ብለዋል፡፡
ችሎቱም ‹‹ለአንድ ወር የለንም›› ካሉ በኋላ 15 የአቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለግንቦት 13፣ 14 እና 17 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡

tirsdag 10. mars 2015

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ቅጣት ተላለፈባቸው


Habitamu
  • በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
  • ᎐ተጨማሪ ቅጣትም ይጠብቃቸዋል
• ‹‹እኛ የደፈርነው ችሎት አሻንጉሊት ችሎት ነው›› አብርሃ ደስታ
• ‹‹ችሎቱ ላይ ያጨበጨብነው በማፌዝ ሳይሆን በምሬት ነው›› የሺዋስ አሰፋ
• ‹‹ፍትህ ተጠምተናል፣ ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ!›› ዳንኤል ሺበሽ
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ከስምንት ወራት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነት እንዲሁም የዓረና ትግራይ ፓርቲዎች አመራሮች ‹ችሎት በመድፈር ወንጀል› ጥፋተኛ በመባላቸው ዛሬ መጋቢት 1/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት በሦስቱ አመራሮች ላይ እያንዳንዳቸው በሰባት ወራት እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል፡፡
የካቲት 26/2007 ዓ.ም ተከሳሾች በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባቸውና ንብረትም እንደተወሰደባቸው በመግለጽ አቅርበውት ለነበረው አቤቱታ ፍርድ ቤቱ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ሙሉ ለሙሉ በመቀበል አቤቱታቸውን ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ 5ኛ ተከሳሽ አቶ የሺዋስ አሰፋ በማጨብጨቡና 3ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታና 4ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሽ ሳይፈቀድላቸው ‹‹ጥሩ ፍርድ፣ ጥሩ ብይን›› በማለት አቶ የሺዋስን በመደገፍ ችሎት ደፍረዋል ተብለው ጥፋተኛ መሰኘታቸው ይታወሳል፡፡
በዚህ መሰረት ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ተሰይሞ በአብርሃ ደስታ፣ በየሺዋስ አሰፋ እና ዳንኤል ሺበሽ ላይ የሰባት ወራት እስራት በእያንዳንዳቸው ላይ ወስኗል፡፡ ሦስቱም ተከሳሾች ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ድጋሜ ችሎት ውስጥ አጨብጭበዋል፡፡ በዚህም ድጋሜ ጥፋተኛ ተብለዋል፤ ከሁለት ቀናት በኋላም የቅጣት ውሳኔ ይወሰንባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሦስቱ ተከሳሾች ‹‹እድል ስጡን እንናገር፣ አቤቱታም አለን ተቀበሉን›› ቢሉም ፍርድ ቤቱ ሊሰማቸው አልፈለገም፡፡ በተለይ ዳንኤል ሺበሺ ‹‹ሌላ አቤቱታ አለኝ፣ ፍርድ ቤቱ ያዳምጠኝ›› ብሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ አሁንም ችሎቱ ላይ እያፌዛችሁ ነው በሚል ጥፋተኛ ሲላቸው ሦስቱም አመራሮች ፍርድ ቤቱን ማስፈቀድ ሳያስፈልጋቸው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
‹‹እኛ የደፈርነው ችሎት አሻንጉሊት ችሎት ነው፡፡ ‹Already› የተደፈረ ችሎት ነው›› ሲል አብርሃ ደስታ ተናግሯል፡፡ በዚህ ጊዜ ዳኞቹ ጣልቃ በመግባት፣ ‹‹የምትናገረው ነገር እንደገና ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የሚወስድህ ጉዳይ ነው፤ ምርመራ ይደረግበታል›› ሲሉ አብርሃ በበኩሉ ‹‹አሁንስ ቢሆን የምናገረውን ፖሊስ እየሰማ አይደለምን?›› ሲል መልሷል፡፡
አቶ የሺዋስ አሰፋ በበኩሉ ‹‹ከስምንት ወር በላይ ታፍነናል፡፡ በህግ አይደለም የተያዝነው፡፡ ደግሞ ማጨብጨባችን በችሎቱ ከማፌዝ ሳይሆን ከምሬት በመነጨ ነው፡፡ ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል፡፡ እኔ ለምሳሌ የሰማያዊ ፓርቲ አባል በመሆኔ ነው የታሰርኩት፡፡›› ብሏል፡፡
አቶ ዳንኤል ሺበሽ ድግሞ ‹‹አሁንም ችሎት ደፍራችኋል ካላችሁ ቅጣቱን ጨምሩብንና ሸኙን፡፡ በእርግጥ ዳኞች ላይ ያለውን ጫና እንረዳለን፡፡›› ሲል ችሎት ውስጥ ተናግሯል፡፡
በዚህ ሁኔታ በተከሳሾችና በችሎቱ መካከል ያለው አለመግባባት ሲጨምር ዳኞቹ መጋቢት 3/2007 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ የቅጣት ውሳኔ እንደሚሰጥ በመጥቀስ ሦስቱ ተከሳሾች ከችሎት በፖሊስ እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ ከችሎት እየወጡ እያሉም አቶ ዳንኤል ሺበሽ ‹‹ፍትህ ተጠምተናል፤ ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ!›› እያለ ችሎቱን ለቅቆ ወጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ሦስቱ ተከሳሾች ከችሎት መውጣታቸውን ተከትሎ፣ ከዚህ ቀደም በማረሚያ ቤቱ ላይ በቀረበው አቤቱታ ዳኞች በሰጡት አስተያየት ላይ አቤቱታ አቅርቦ እንደነበር በማስታወስ አቤቱታው እንዲመዘገብለት የጠየቀው አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ ‹‹በበኩሌ ያሉኝን መረጃዎች እያቀረብኩ ስነ-ስርዓቱን አክብሬ ክርክሩን አቀጥላለሁ›› ሲል ተናግሯል፡፡

tirsdag 24. februar 2015

ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር – ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም

የጎረቤት ኬንያ ዳኛ ለኬንያ መንግሥት አስፈጻሚው ክፍል ልኩን ነገረው፤ ሕገ መንግሥቱን በመርፌ አስተኝተህ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ሕግ ለማውጣት አትችልም፤ ስለዚህም የሰነዘርኸውን የጉልበት ሕግ አንሣ፤ አለው፤ ዳኛ አይጥፋ! ሌላ ቢቀር ከጎረቤት ዳኝነትን እንስማ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር ስንት ጋዜጠኛ፣ ስንት የሃይማኖትና ስንት የፖሊቲካ መሪዎች ከየወህኒ ቤቱ ይወጡ ነበር! ሁላችንም እንደልባችን ሳንፈራ፣ ሳንፈራራ በሙሉ ነጻነት ችግሮቻችንን የወያኔን ጭቆና ጨምሮ ለመወያየትና መፍትሔዎችን ለመለዋወጥ የምንችልበት መድረክ፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ራድዮና ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖረን ነበር፤ ስንት ሰው ሥራ ያገኝ ነበር፡፡
ከሁሉም በላይ በየመንገዱ ጠመንጃ የያዘ ሊያስፈራራን የሚሞክር ሆድአደር እያየን፣ እንደዚሁም በየጫካው ያሉትን እያሰብን ሰላማችንን ከምናጣ አበባውን ትተን፣ ሩዙን ትተን፣ የተወደደልንን ጤፋችንን እያመረትን አዲስ ኑሮ ብንጀምር የተሻለ ነበር፡፡
ግን አንድ እንቅፋት አለብን፤ እነዚህ ከየኪዮስኩ እውቀት ገዝተን አዋቂዎች ሆነናል የሚሉት እንትኖች እንመጀመሪያ ችግሩ እንዲገባቸው፣ ሁለተኛ መፍትሔው እንዲገባቸው፣ ሦስተኛ ጉልበትና እውቀት አንድ አለመሆናቸውን ብቻ ሳይሆን በጉልበት እውቀት የማይገኝ መሆኑን ማሳመን በረዶ እየወረደ የስሜን ተራራን መውጣት ነው፤ በረዶ ሳይኖር ወጥቼዋለሁ!
እነዚህን የጉልበት አዋቂዎች — ስለሽማጌሌዎችና አሮጊቶች ሳያስቡ፣ ስለመብራት ኃይል ሳያስቡ፣ ስለውሀ ሳያስቡ ሁሉም በጉልበት ፎቅ ይውጣ የሚሉ! ይባስ ብለው ለእስረኛውም ፎቅ እየሠሩለት ውጣ! ሊሉት ነው!
እነዚህ የጉልበት አዋቂዎች የአበሻ ኑሮ፣ ቡናው፣ ሙቀጫው፣ ምጣዱ፣ በርበሬው፣ ቁሌቱ፣ ቄጤማው፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ ኧረ ስንቱ! ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው! እናውቃለን ስለሚሉ እንዴትስ ይማራለ? በእውነት ለመማር ቢፈልጉስ ስንት ዓመት ሊያስፈልጋቸው ነው! እግዚአብሔር እንሱንም እኛንም በምሕረቱ ይጎብኘን! የሚያስተምር ጎረቤት አያሳጣን!

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን አስታወቁ

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡
ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች ‹‹መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ›› እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡
ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና ጎጃም አካባቢዎች የዛሬ አራት ወር ገደማ በፖሊስ ታስረው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ጠበቃቸው በተደረገባቸው ክልከላ ምክንያት ተጠርጣሪዎቹን ካገኟቸው 2 ወር እንደሞላቸው ተናግረዋል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ አግባው ሰጠኝ እየተፈጸመበት ያለውን የመብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አድማውን ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መሰረት አመራሮቹ የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

fredag 20. februar 2015

አረና ትግራይ ኢትዮጵያ ውስጥ በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ምርጫ ያስመዘገባቸው እጩዎቹ ራሳቸውን ከምርጫው ለማግለል እየተገደዱ መሆኑን አስታወቀ።

አረና ለፌደራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ከ100 በላይ እጩዎቹ ቢመዘገቡም በተለያዩ አካባቢዎች በደረሰባቸው ጫና ምክንያት በርካቶች ከውድድር መውጣታቸውን ፓርቲው አመልክቷል። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ሳይቀሩ ካርድ የለም ተብለው እንዲመለሱ መደረጉን የፓርቲው የሕዝብ ግኑኙነት ለዶቼቬለ ተናግረዋል።
አረና ትግራይ ኢትዮጵያ ውስጥ በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ምርጫ ያስመዘገባቸው እጩዎቹ ራሳቸውን ከምርጫው ለማግለል እየተገደዱ መሆኑን አስታወቀ። አረና ለፌደራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ከ100 በላይ እጩዎቹ ቢመዘገቡም በተለያዩ አካባቢዎች በደረሰባቸው ጫና ምክንያት በርካቶች ከውድድር መውጣታቸውን ፓርቲው አመልክቷል። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ሳይቀሩ ካርድ የለም ተብለው እንዲመለሱ መደረጉን የፓርቲው የሕዝብ ግኑኙነት ለዶቼቬለ ተናግረዋል። የክልሉ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን የአረናን አቤቱታ መሠረተ ቢስ ሲሉ አጣጥለዋል። ዝርዝሩን ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር አዘጋጅቶታል ።

søndag 1. februar 2015

ሬድዋን ሁሴንና የወደቀው ክሱ !


በኢትዮጵያችን ህግ ትርጉሟን አጥታ፤ፍትህም ተዋርዳ ከተጣለች የህወሃትን እድሜ ብታስቆጥርም እነርሱ ግን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ስለ ህግ የበላይነት ማውራታቸውን አላቆሙም። እነዚህ ቡድኖች የህግ የበላይነት ሲሉ እነርሱ ከፍ ብለው ከህግ በላይ፤ ከእነርሱ መንደር ያለሆነው ደግሞ ዝቅ ብሎ ከሥር ከጫማቸው ሥር ሁኖ እነርሱን ተሸክሞ የሚኖርበትን ሥርዓት ማስጠበቅ የሚችለውን ህግ ነው። እናንተን መሸከም ከበደኝ፤ ቀንበራችሁ ሰበረኝ የሚል ሰው ከተገኘ የሚጠብቀው ፍርድ “አሸባሪነት” ነው። ይህ የክፉዎችና የልበ ደንዳኖች ፍርድ ፍትህ ተብሎ በህወህቶች መንደር ይወደሳል። መፅሃፍ እንዲህ ይላል “ክፍዎች ሰዎች ፍርድን አያስተውሉም”። ህወሃቶች ባወጧቸው ህጎች የስንት ንፁሃን ዜጎች ቤት እንደፈረሰ፤ ስንት ህፃናት አሳዳጊ አልባ እንደሆኑ፤ ስንቶች አገራችውን ትተው ተሰደው እንደጠፉ ቆጥረን አንዘልቀውም። በህወሃት መንደር ህግ ዜጎችን ማጥቂያ እና ማስጨነቂያ መሣሪያ እንጂ የፍትህ ማስከበሪያ መሳሪያ አይደለም። በህወሃት ህግ ብዙ ዜጎች ጠፍተዋል፤ ብዙዎች ደግሞ በብዙ ጭንቀት እና መከራ ውስጥ ይገኛሉ።

በህወሃት መንደር የተሰባሰቡ ግለሰቦች እንደምን ያለ ብርቱ ጭለማ እና ድንቁርና ውስጥ እንደሚገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ማንሳት እንችላለን። ለአሁን ግን ማሰብ ካቆሙ ቅጥረኞች መካከል ሬድዋን ሁሴን የተባለው ግለሰብ የሆነውን እንመልከት። ሬድዋን ሁሴን፤ ጌቶቹ እና ሌሎች መሰሎቹ ያሉበትን ዘመን ረስተው ወይም መረዳት ተስኗቸው፤ ከስልጣኔ መንገድም ወጥተው እንዲሁ በጭለማ ዓለም እየተደናበሩ ይገኛሉ። ሬድዋን ሁሴን ያለበትን ዘመንና የያዘው የህዝብ ስልጣን የሚያስከትልበትን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤት መገንዘብ ስለተሳነው ቀና ብሎ ተናገረኝ ባላው ወጣት ላይ በአሜሪካን አገር ክስ መመሥረቱን ስንሰማ በብርቱ ተደንቀናል። አገራችንም በእንደነዚህ ዓይነት ማስተዋል በጎደላቸው ግለሰቦች የምትመራ መሆኑም በእጅጉ ያሳዝነናል።

ሬድዋን ሁሴንን በቨርጂኒያ አገረ ግዛት ያገኘው ወጣት ህወሃቶች በወገኖቹ ላይ የጫኑባቸው ሸክም ያሳመመው፤ በዚህም ህመም የተቆጣ ቁጣውንም በሰላም የመግለፅ መብቱ ያለ ገደብ የተከበረባት አገር ውስጥ ኗሪ ነው። ሬዲዋን ሁሴንን የመሰለ ራሱን ለምናምንቴ ነገር አሳልፎ የሸጠ ትንሽ ግለሰብ ይቅርና የሃያሏ አገር አሜሪካን ፕሬዝዳንትም ብዙ ወቀሳና ስድብ ይደርስበታል።ፕሬዝዳንቱም የህዝብ ተቀጣሪ መሆኑን ስለሚያውቅ ተወቀስኩ ወይም አንድ ዜጋ ተናገረኝ ብሎ የበቀል ሰይፉን አይመዝም። ፕሬዝዳንቱ ተሰደብኩ ብሎ ክፉ ቢናገር የሚከተለው መዘዝ ከስድቡ የበለጠ ጉዳት ስለሚያደርስበት ስድቡን መቻል እና መሸከም የሥራው አንዱ አካል ይሆናል።ህግ ባለበት አገር የአገሩ መሪ ህዝቡን ፈርቶ ይኖራል እንጂ፤ ህዝብ መሪውን ፈርቶ አይኖርም። ሬዲዋንና መሰሎቹ ግን እንዲህ አይደሉም። ህዝብን ረግጠውና አስፈራርተው መኖር የጎበዝ ተግባር ነው ብለው አምነው ተቀብለዋል።

ህወሃት ትንሹንም ትልቁንም ፈርቶ፤ ፍርሃቱ በወለደው ጭካኔ ዜጎችን ሁሉ አስሮ መኖር ልማዱ ሁኗል። በኢትዮጵያ ዜጎች ህወሃቶችን ፈርተው፤ ህወሃቶችም ዜጎችን አስፈራርተው የሚኖሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄ ሁኔታ ለማንም ወይም ለምንም እንደማይበጅ ለህወሃቶች ብንነግራቸውም ልቦናቸው በትዕቢት ታውሯልና አይሰሙንም። ሬድዋን ሁሴንም የዚህ መራራ ትዕቢት ትሩፋት ነው። እንደምን ሁኖ ቀና ብለው ያዩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ይናገሩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ስሜ በገበያ መሃል ይነሳል የሚል ትዕቢት ስለተፀናወተው ክስ መሠረተ፤ ክሱ ግን በህግ ፊት ሚዛን የማይደፋ በመሆኑ በአቃቤ ህጉ ውድቅ ተደረገ። ሬዲዋንም የፍትህን መራራ ፅዋ ተጎንጭቶ ሊውጣት ግድ ሆነበት። የህወሃት ቅጥረኞችና ህወሃቶች ውድቅ ከሆነው ከሬድዋን ህሴን ክስ ልትማሩ የሚገባችሁ የህግ የበላይነት በሰፈነበት አገር እናንተ ከተራው ዜጎች እኩል እንጂ የበላይ ልትሆኑ እንደማትችሉ፤ ከመጋረጃው ጀርባ ሁናችሁ ፍትህን የምትጠመዝዙበት እጃችሁ እንደሚታሰር እና ገና ወደፊት ደግሞ የእጃችሁን እንደምታገኙ ነው። እናንተን ከተራው ዜጋ እኩል የሚያደርግ ህግ ሲፈጠር የታጠቃችሁት ጠብመንጂያ የሸንበቆ ምርኩዝ፤ የመኖሪያ ድንኳን የሆናችሁ ማን አለብኝነታችሁ ደግሞ ፀሃይ እንዳየው ጤዛ እንደሚተን ልብ ልትሉ ይገባል። ሬዲዋንን የተናገረው ወጣት ኢትዮጵያ ውስጥ ሁኖ ቢሆን ኑሮ ዛሬ እነሬዳዋን ፈተው በሚለቋቸው ውሾች ሊደርስበት የሚችለውን ስቃይ ስናስበው ይዘገንነናል። ከባህር ማዶ መሆኑ ከሥጋዊ ስቃይ አድኖታል።

እንግዲህ ህወሃቶች የምትፈፅሟቸው ግፎች በየደረሳችሁበት እየተከታተሉ እረፍት ማሳጣታቸውን የሚያቆሙ አይሆንም። የምትሠሯቸው ግፎች የሚያሳድዱት እናንተን ብቻ አይደለም። ከእናንተ አብራክ የሚፈጠሩ ልጆቻችሁንም ጭምር የክፉ ሥራዎቻችሁ ሰለባዎች ከመሆን አያመልጡም። ልጆቻችሁ ተሳቀው ከህዝብ ዓይንና ጆሮ ተደብቀው መኖር ዕድል ፈንታቸው ይሆናል። እናንተ የምትፈፅሙት ወንጀል ለልጆቻችሁ ኩራት ሳይሆን እፍረት፤ ክብር ሳይሆን ውረደት ሁኖ ይቆያቸዋል። ቢያንስ ለልጆቻችሁ ሠላም ስትሉ ከእኩይ ድርጊታችሁ መታቀብ ይሻላችሁ ነበር። እናንተ ግን ለትውልዱ ሠላም የሚሻለውን ትታችሁ የጥፋቱንና የደም መፋሰሱን መንገድ መርጣችኋልና ወዮታ አለባችሁ።

እናንተን መታገል ከስጋና ከደም ጋር የሚደረግ ትግል ብቻ አይደለም። የምትፈፅሟቸው ግፎች ከሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈልቁ ብቻ አይመስልም።ከእናንተ ጋር የሚሰራ ሌላ የማይታይ የክፋት አባት ያለ እስከሚመስለን ድረስ ግፋችሁ አንገፍግፎናል። ይህን ግፍ ዝም ብለን የምናይ አይመሰላችሁ። ሊከፈል የሚገባውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተናል። ወጣቶችም ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱባቸው ኮረብቶች ላይ ተሰማርተዋል። ክፉውን ለመቃወም፤ ደም አፍሳሹን ለማስቆም፤ ሌባውን ተው ለማለት፤ ትዕቢተኛውን አደብ ለማስያዝ፤ የነፃነት ቀበኛውን ለማስተማር ሰይፋቸው ከአፎቱ ተስማምቶ ተዘጋጅቷል።

የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች ሆይ !

ህወሃቶች በዜጎችቻን ላይ የሚፈፅሙትን ግፍ ለእናንተ መንገር ለቀባሪው እንደ ማርዳት ይሆንብናል።የእነዚህ ቡድኖች ግፍ ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰሰ ነው።የአገሪቷን ታሪክ አንድ በአንድ ለማጥፋት እየሠሩ ይገኛሉ-በየቦታው በእሳት የሚቃጠሉት ታሪካዊ አምባዎቻችን የአገሪቷን ታሪክ የማጥፋት ዘመቻ አካል ነው።ዜጎች አገር አልባ እንዲሆኑ ተደርገዋል፤ አብሮ በኖረው ህዝብ መካከል የሚዘራው የጥላቻ ዘር ለአገራችን አደጋ ሁኖ ተደንቅሯል። አገራችን ታሪኳ በሚመሰክርላት ሥፍራ ላይ እንዳትሆን፤ ለአፍሪካ ቀንድም ሆነ በአጠቃላይ ለዓለም ሠላም መጫወት የሚግባትን ሚና እንዳታከናውን ተደርጋለች። በተቃራኒው የግጭት አምባ፤ የችጋር ምሳሌ፤ የስደት ምልክት ሁና ከውዳቂ መንግስታት ተርታ ገብታለች። ይሄ ሁሉ እርግማን በህወሃት ምክንያት የመጣ ነው።

እኛ በአገራችን ላይ የተተከለውን ህወሃት የተባለውን እርግማን ነቅለን ለመጣል የምንችለውን ሁሉ እያደርገን ነው። ህወሃቶች የነፃነትን ዋጋ ተረድተው፤ ለፍትህ ክብር ሰጥተው፤ ዜጎችን አክብረው፤እኛም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር እኩል ነን። ከማንም አንበልጥም፤ ሌላውም ከእኛ አያንስም ብለው በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመወያየት ፍርሃታቸው እና ድንቁርናቸው ቢፈቅድላቸው ለሁላችንም መልካም ነበር። ይህ መልካም ነገር ግን የእኛ ምኞት ብቻ ሁኖ ቀርቷል።ህወሃቶች የተፀናወታችው ትዕቢት የሰይጣን ትዕቢት ስለሆነ እንዲሁ በቀላሉ በጄ የሚሉ አይሆኑም። እኛ የቀረን አንድ መንገድ በማንኛውም መንገድ አገራችንን ከጥፋት ማዳን ብቻ ነው። ይህም ታሪካዊ ግዴታችን ሁኗል።

ይህን አገርን የማዳን ታሪካዊ ግዴታ የዚህ ቡድን ወይም ደግሞ የዚያ አካል ብቻ ተደርጎ መወሰድ ያለበት ተግባር አይደለም። እያንዳንዱ ማሰብ የሚችል እና ለራሱ ትንሽ ክብር ያለው ዜጋ ሁሉ ኢትዮጵያን ለመታደግ የሚችለውን ጠጠር መወረወር ይጠበቅበታል። ኢትዮጵያ ሬድዋን ሁሴንን በመሳሰሉ ምናምንቴዎች ስትዋረድ እጅን አጣምሮ ቁሞ መታዘብ ትክክለኛ ተግባር አይሆንም። የአገሪቷ ድሃ ዜጎች ስቃያቸው በዝቶ እና ጭንቀታቸው ልክ አጥቶ እያየን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ካሉ ዜጎች ጋር መተባበሪያ ግዜው አሁን ነው።

እኛ አርበኞች-ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ አገራችን ከገባችበት የውርደት አዘቅት ውስጥ ለማውጣት የጀመርነውን ትግል እለት እለት እያደስነው፤ እለት እለት እያሰፋነው፤ እለት እለት እያሳደግነው ቀጥለናል። እኛ ዓይናችን እያየ ህዝባችን አይዋረድም፤ አገራችንም ከሥፍራዋ በታች ስትሆን ዝም አንልም።የሚከፈለውን ማንኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፍለ አናቅማም። በአያት ቅደመ አያቶቻችን ደም ተከብራ የኖረች አገር ዳግም በእኛ ደም ተከብራ ትኖራለች። ቀጣዩ ትውልድም የተከበረች አገር ተርክቦ፤ እርሱም ተከብሮ ይኖር ዘንድ እኛ እንሰራለን እግዚአብሄርም ያከናውንልናል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

lørdag 31. januar 2015

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን፡፡ አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል፡፡UDJ/Andinet party logo
ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው፡፡ ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል፡፡ በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን፡፡
ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል፡፡ በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡
ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!!!

tirsdag 27. januar 2015

አቶ ትግስቱ አወሉ በአንድነት የክልል አመራሮች ላይ በስልክ ዛቻ እየፈፀሙ መሆኑ ተገለፀ፡፡


የአንድነት ፓርቲ ሰሞኑን በኢህአዲግና ምርጫ ቦርድ ከፍተኛ ዘመቻ ተከፍቶበት እንደሚገኝ መላው ኢትዮጵያዊ እየተከታተለው ያለ እውነታ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከምርጫ ቦርድ ጋር በመሆን አንድነት ፓርቲን ለመፈረካከስ ከሚሰሩት ግለሰቦች መካከል አቶ ትግስቱ አወሉ የተባሉና የቀድሞ የአንድነት አባል በአሁኑ ሰዓት እራሳቸውን ፕሬዝደንት አድርገው ከምርጫ ቦርድ ጋር በጋራ በመስራት ላይ ያሉ ግለሰብ በ16/05/2007 ዓ.ም ላደረጉት ህገ-ወጥ ጉባኤ ተልእኳቸውን ለማስፈፀም በየክፍለሀገሩ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ የጉባኤ አባላትን በስልክና በአካል በመሄድ ለዚህ ህገ-ወጥ አንድነት ፓርቲ ነኝ ባይ ጉባኤ እንዲገኙ በማግባባት፤ከመንግስት ፈሰስ በተደረገላቸው ገንዘብ በመደለል እንዲሁም እንቢ ያሉ ግለሰቦችን ‹‹መንግስት ከኔ ጎን ነው እንቢ ካልክ/ሽ እርምጃ እንወስዳለን፤…..ወዘተ›› ማስፈራሪያ ሲጠቀሙ እንደነበር በየአካባቢው የሚገኙ የአንድነት አባላት ሰሞኑን ሲገልፁ የነበረ ሲሆን ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት ግለሰቡ በደቡብ ወሎ የአንድነት መዋቅር በሚገኝባቸው ሐይቅ፤ወረባቦ፤ደሴ፤ኮምቦልቻ፤ኩታበር …….የመሳሰሉት ወረዳዎች የሚገኙ የአንድነት የወረዳ አመራሮች ጋር ስልክ በመደወል ከፍተኛ መስፈራራትና ዛቻ የተቀላቀለበት ድርጊት መፈፀማቸውን ከየወረዳዎቹ ያሉ የአንድነት አመራሮች ሪፖርት አድርደዋል፡፡ ግለሰቡ አንድነት ፓርቲ የኔ ነው፤እኔም ነኝ የምመራው፤ በኔ አስተዳደር ስር ሆናችሁ ላለመሳተፍ ከወሰናችሁ፤ በመንግስት በኩል ከፍተኛ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅት ተደርጓል›› ….ወዘተ የሚል ማስፈራሪያ እንደሚያሰሙ ገልፀዋል፡፡ አባላቶቹ አያይዘውም ‹‹እኛ አንድነት አንድ እንጂ ሁለት አይደለም፤ህጋዊ የሆነው አንድነት ፓርቲ በተገቢው ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ባለበት አግባብ መንግስትና ምርጫ ቦርድ ፓርቲውን ለመበታተን ለሚያደርጉት ዘመቻ ተገዢ አንሆንም፤ሰላማዊ ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አቶ ትግስቱ አወሉ በህጋዊውና በትክክለኛው የአንድነት ፓርቲ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ እራሳቸውን እጩ አድርገው አቅርበው በመሳተፍ የራሳቸውን አንድ ድምፅ ብቻ አግኝተው መውደቃቸው የሚታወስ ነው፡

onsdag 21. januar 2015

ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀው ውይይት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ

ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀውን ይህን ውይይት በርካቶች በአካል በስብሰባው ቦታ ተገኝተው ከተከታተሉት ታዳሚዎች ባሻገር በርካቶች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች በስካይፒ የተከትሉት ሲሆን፤ ፓናሊስቶቹ ባቀረቧቸው ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሂዷል።
ፕሮፌሰር መስፍን  ሰማያዊ ፓርቱ እና በሰሜን አሜሪካ የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ኮሚቴ በመተባበር ያዘጋጁትን ውይይት ሲከፍቱ
ሁላችንም ስንለወጥ ነው ለውጥ የሚመጣው ብለዋል  ፕሮፌሰር መስፍን፤ ከጣሊያን ጊዜ አንስቶ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረስ ባንዳው፣ፖሊሱ፣ባለስልጣኑ ሁሉ በመሸጦነት ማለፋቸውን በማውሳት፤ አንድ ትውልድ ይህን የመሸጦነት ባህል እየተባበረ ከሄደ ለውጥ እንደማይመጣ በአንጽንኦት ተናግረዋል።
ተከታዩ ተናጋሪ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ደግሞ፦‹ለህወሓቶች ፖለቲካ ማለት ወዳጅና ጠላት የሚለይበትና ፍልሚያ የሚደረግበት ነው ፡፡ አንድ የናዚ ሰውም ፦ፖለቲካ ማለት ወዳጅና ጠላት የሚለይበት ሜዳ ነው>> ነው የሚለው፡፡ብለዋል።
ህወሀቶች ያለ ጠላት መንቀሳቀስ አይችሉም፡፡ያሉት ዶክተር ዳኛቸው፤ ድህነትንም ጠላት ብለውታል፡፡ ሲጀመር እኛ እና እነሱ ይባልና- ጠላትና ወዳጅ ወደሚለው ያድጋል፡፡›› ብለዋል። ሁላችንም በሀገራችን የባለቤትነት መብት ቢገባንም የሀገሪቱ ፖለቲካ ዝግ ሆኗል ያሉት ዶክተር ዳኛቸው፤ ውድድር በሌለበት ቦታ ፍትሐዊ ምርጫ ማድረግ እንደማይቻል ገልፀዋል።
የአዲሲቷ ኢትዮጰያ የጋራ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው፤ በጎሳና በዘር ተከፋፈግለናል፤ ሀገራችንን ለመቀየር ከፈለግን ለውጡ ከራሳችን መጀመር አለበት ብለዋል።
እኛ ለሀገራችን ዋጋ ካልከፈልን፤ማንም ለኢትዮጰያ ዋጋ ሊከፍልልን አይችልም ብለዋል-አቶ ኦባንግ።
የዞን 9 ጦማርያን አባል የሆነችው ሶልያና ሽመልስ በበኩሏ ትንሽ የሚመስሉ ጥረቶችን ማድነቅ እንደሚያስፈልግ በመጥቀስ፤ ቀደም ሲል ጠቀሜታው ብዙም ግምት ያልተሰጠውንና በአሁኑ ወቅት ተጽእኖ እየፈጠረ ያለውን በኢንተርኔት መረጃ የመለዋወጥን እና የመጻፍን ጉዳይ በተደራጀ መልኩ መጠቀም እንደሚያስፈልግ መክራለች።
በምርጫ 97 ወቅት የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር የነበሩት ዳኛ ፍሬህይወት ሳሙኤል በበኩላቸው ኢትዮጰያ ውስጥ የህግ የበላይነት እንደሌለ ምሳሌዎችን በመጥቀስ ተናግረዋል።
ኢትዮጰያ ውስጥ ወደ እስር ቤት የተወረወሩት አንድም በፖለቲካ የተሳተፉ አለያም ድሆች ናቸው ያሉት ዳኛ ፍሬህይወት፤ “የሀብታም ክስ ከፖሊስ አልፎ ፍርድ ቤት አይደርስም ብለዋል።
“ለውጥ ይመጣል፡፡ ለውጥ ይሸተኛል”በማለት ንግግራቸውን የጀመሩት ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ናቸው።
ለውጡ እንደስከዛሬው እንዳይከሽፍ ግን ፖለቲከኞችና የፖለቲካ ቡድኖችበራሳችን ላይ አብዮት ማምጣት አለብን፡፡ያሉት ኢንጂነር ይልቃል  ከእስካሁኑ የተለየ ለውጥ እንዲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ማድረግ አለብን›› ብለዋል።