torsdag 27. februar 2014

አብርሃ ደስታ… ታስሮ ተፈታ!!


EMF – በትግራይ ውስጥ የሚደረጉ ግፍ እና በደሎችን ያለመሰለስ በማጋለጡ ይታወቃል:: ለሰብአዊ መብቶች መከበር በመቆሙ ከህወሃት ሰዎች ተደጋጋሚ ማስፈራሪያ እና ዛቻዎች ሲደርሱበት ነበር:: ባለፈው ሳምንት ቃሊቲን ለመጎብኘት የፖለቲካ እስረኞችንም ለመጠየቅ ወደ አዲስ አበባ ሄዶ በነበረበት ወቅት “እንዴት የፖለቲካ እስረኛ ለመጠየቅ ከትግራይ ድረስ መጣህ?” በሚልም ለእስር ዳርገውታል:: ሁኔታውን እራሱ አብርሃ ደስታ እንዲህ በማለት ገልጾታል::
አዲስ አበባ ነበርኩ። ሰኞ ጧት ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ርእዮት አለሙ ለመጠየቅ ቃሊቲ ማረምያቤት ሄድኩኝ። ጥበቃዎቹ ወደ ማረምያቤቱ አስተዳዳሪ ወሰዱኝ። አስተዳዳሪው ምርመራ ይሁን ዛቻ በማይታወቅ መልኩ ካስፈራራኝና ከሰደበኝ በኋላ ከማረምያ ቤቱ ተባረርኩ። አስተዳዳሪው “አንተ ከትግራይ አክራሪ አማራዎችን ለመጠየቅ ስትመጣ አታፍርም?!” አለኝ። ከፈለኩ ብሄር ብመጣም የፈለኩትን ሰው የመጠየቅ መብት አለኝ። የታሰረ ሰው መጠየቅ አያሳፍርም” መለስኩለት። ካሁን በኋላ “ወደ ቃሊቲ የምትገባው ታስረህ ካልሆነ በቀር እነ አንዱኣለምን ለማየት ድርስ አትላትም!” ብሎ ፖሊሶችን እንዲያስወጡኝ አዘዘ።
ወደ ቂሊንጦ ማረምያ ቤት ተጓዝኩ፤ ኡስታዝ አቡበክር አህመድን ለመጠየቅ። “አሸባሪ ለመጠየቅ መጣ” ተብዬ ለሦስት ሰዓታት ታሰርኩ። የቂሊንጦ ማረምያቤት ዋና አስተዳዳሪ እምባዬ ህቡዕ “አሸባሪዎችን ለማበረታታት መጣህ፣ ማረምያቤቱን ለመበጥበጥ ነው የመጣኸው። እንዳውም አሁን በማረምያቤቱ ረብሻ ተነስቷል። ስለዚህ ይታሰር” ብሎ በማዘዙ ወህኒቤት ዉስጥ ቆየሁ።
 ዝርዝር ጉዳዩን ለመፃፍ እሞክራለሁ። አንዱኣለም አራጌና ርእዮት አለሙን አላየኋቸውም። አቡበክር አህመድ (ና ሌሎች ጉደኞቹ) ግን አግኝቻቸዋለሁኝ። እነ አቡበክር አህመድን በማግኘቴ ደስ ብሎኛል።

onsdag 26. februar 2014

ግብፅ በህዳሴው ግድብ ላይ የጀመረችውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ልታላብሰው ነው

February 26/2014


-



















-ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነካቢኔያቸው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ

የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ የጀመረውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ለማላበስ አዲስ እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው፡፡

ከወደ ግብፅ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የግብፅ የውኃና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ይህንን አዲስ እንቅስቃሴ ያስተባብራሉ፡፡

ከዚህ ቀደም ግድቡን በተመለከተ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተገትቶ፣ አዲሱ ዘመቻ ፊቱን ወደ ጣሊያንና ኖርዌይ አዙሯል፡፡ ከዚያም ወደተለያዩ አገሮች ይቀጥላል፡፡

ባለፈው ሳምንት የውኃ ሚኒስትሩ መሐመድ አብዱል ሙታሊብና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነቢል ፋህሚ ወደ ጣሊያን ጉዞ አድርገዋል፡፡ የግብፅ መንግሥት ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ዋነኛ ሸሪክና የግድቡ ግንባታ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ባሉዋት ጣሊያን የተደረገው ጉብኝት ስኬታማ ነበር ብለዋል፡፡

የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ የግድቡን ጥናትና ግንባታ የሚያካሂድ በመሆኑ፣ ጣሊያን የግብፆች የአዲሱ ዘመቻ ዓላማ መሆኗ እየተነገረ ነው፡፡ የውኃ ሚኒስትሩ ሙታሊብ ለግብፅ ሚዲያዎች እንደገለጹት፣ የጣሊያን ጉብኝት ግቡን በመምታቱ ወደ ሌሎች አገሮችም ጉዞው ይቀጥላል፡፡ ምንም እንኳ የተገኘው ስኬት ምን እንደሆነ ባይብራራም፣ ሙታሊብ ለጣሊያን መንግሥት ባለሥልጣናት በግድቡ ምክንያት ግብፅ ሊደርስባት የሚችለውን የውኃ ችግር ማስረዳታቸውን፣ የጣሊያን ባሥልጣናትም ችግሩን አሁን ገና መስማታቸውን መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡ የሚቀጥለው ጉዞም ለህዳሴው ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ታደርጋለች ባሉዋት ኖርዌይ እንደሚሆን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ኖርዌይ ለግድቡ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ መቼና የት እንደሰጠች ግን አላብራሩም፡፡ ግብፆች ለግድቡ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ ከሚያደርጉ አገሮች መካከል አንዷ ኖርዌይ ናት በማለት ሌሎችም አገሮች ዕርዳታ ይሰጣሉ የሚል አንድምታ ያለው አስተያየት መሰንዘራቸው ተሰምቷል፡፡ 

የግብፅ መንግሥት የሚቀጥለው ዕርምጃ በተለያዩ አገሮች የሚደረግ ጉዞ ሲሆን፣ በየአገሮቹም የግብፅን አቋም በሰፊው ማስተዋወቅ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የዚህ ጉዞ ዓላማ ለግብፅ ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ ማስገኘት መሆኑ ተወስቷል፡፡ ከእነዚህ ጉዞዎች ለግብፅ ድጋፍ ማስገኘት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ማሳጣትም ነው ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ ግድቡ ግብፅን አይጐዳም እያለች ባለችበት ወቅት፣ ግብፆች ግን ይህ ግድብ በግብፅ ህልውና ላይ አደጋ የጋረጠ ነው በማለት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማሳወቅ መዘጋጀታው ተሰምቷል፡፡

ለተመድና ለአፍሪካ ኅብረት የሚቀርበው አቤቱታ ከፕሬዚዳንታዊው ምርጫ በኋላ የሚመሠረተው መንግሥት ተግባር እንዲሆን ወደጐን ተገፍቶ፣ አሁን የተያዘው በተለይ በአውሮፓ አገሮች ውስጥ ሰፊ ዘመቻ መጀመር እንደሆነ ሾልከው የወጡ ሪፖርቶች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዓባይ ወንዝ ተፋሰስ አገሮች ውስጥ ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ በግድቡ ላይ ጥያቄ ለማስነሳት ሌላ ዘመቻ መታቀዱም ይሰማል፡፡ ሰሞኑን የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋህሚ ነቢል በታንዛኒያ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ጉብኝቱንም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጃካያ ኪክዊቴ ማንም አገር ግድብ ሲገነባ የተፋሰስ አገሮችን ማማከር አለበት ማለታቸው ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡     

የግብፅ የውኃ ሚኒስትር ሙታሊብ መንግሥታቸው በርካታ አማራጮችን በመያዝ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ ስምምነት መድረሱን በይፋ አረጋግጠዋል፡፡ በዚህም መሠረት በበርካታ አገሮች ግድቡ ግብፅን እንዴት እንደሚጐዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ይሠራሉ ብለዋል፡፡ የግብፅን ተለዋዋጭ አቋምና ዕረፍት የለሽ እንቅስቃሴ የሚከታተሉ ወገኖች ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ለአፀፋው ተዘጋጅቷል ወይ በማለት ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡ ኢትዮጵያ ግድቡ ከራሷ አልፎ ለአካባቢው አገሮች የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጐት መሟላት ወሳኝ መሆኑንና የግድቡን የጥራት ደረጃ በሚገባ ማሳየት አለባት ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እውነታውን ይዛ በግብፅ ፕሮፓጋንዳ መበለጥ የለባትም በማለት ያስረዳሉ፡፡ 

ይህ በዚህ እንዳለ የግብፅ ጊዜያዊ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሐዚም አል ቤብላዊና የሚመሩት ካቢኔ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በአገሪቱ ሊካሄድ የሁለት ወራት ዕድሜ ሲቀረው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንታዊው ምርጫ እስኪከናወን ድረስ አገሪቱን እንዲያስተዳድር የተመረጠው የግብፅ ጊዜያዊ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትርና የሚመሩት ካቢኔ ባለፈው ሰኞ የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ለጊዜያዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት ማስገባታቸውን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ካቢኔያቸው የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ያስገቡበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለጊዜው የተባለ ነገር የለም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገሪቱ መንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ፣ እሳቸውና ካቢኔያቸው የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄያቸውን ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት አሊ መንሱር እንዳስገቡ ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥልጣን መልቀቂያውን ለምን እንዳስገቡ ባይገልጹም፣ ከካቢኔያቸው ጋር የ15 ደቂቃ ውይይት አድርገው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ‹‹በግብፅ መንግሥት ውስጥ ብቻ ለውጥ ማምጣት ትርጉም የለውም፡፡ የግብፅ ሕዝብ የሚፈልገውንና የሚመኘውን ለመሆን በራሱ መጣር አለበት፤›› ሲሉ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር አል ቤብላዊ፣ ‹‹ግብፅ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሆነች ሁሉ ሊጨበጡ የሚገባቸው ትልልቅ ዕድሎች እየተበላሹባት ነው፡፡ ስለዚህ ጊዜው ለአገራችን ስንል መስዋዕትነት የምንከፍልበት ነው፤›› ብለዋል፡፡

በሙያቸው ኢኮኖሚስት የሆኑት ቤብላዊ የግብፅ ሕዝብ አገሬ ምን አደረገችልኝ ከማለት ባለፈ፣ ለአገሬ ምን አደረግኩ ብሎ መጠየቅ እንዳለበት ገልጸው፣ የአጭር ደቂቃ መግለጫቸውን አጠናቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚመሩት ካቢኔ በአጠቃላይ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ከፍተኛ ትችት ሲጐርፍባቸው ነበር በማለት የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ይገልጻሉ፡፡ በበርካታ መገናኛ ብዙኃን ትችቶችም ሲወርዱባቸው ነበር፡፡ 

የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲን አሸባሪ ብሎ ለመፈረጅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ረጅም ጊዜ አጥፍተዋል፡፡ በቅርቡ በፀደቀው የደመወዝ ስኬል የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሠራተኞች እንዳይካተቱ ማድረጋቸው፣ በአገሪቱ ውጥረትና የሽብር ጥቃቶች እንዲንሰራፉ አድርገዋል በማለት ይተቿቸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪና የጨርቃ ጨርቅ ሠራተኞች፣ ዝቅተኛ ደረጃ ያላቸው የፖሊስ አባላት፣ የፖስታ ቤት ሠራተኞች፣ እንዲሁም የሕክምና ዶክተሮች በተቃውሞ ውስጥ እየተሳተፉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩና ካቢኔያቸው ያቀረቡትን መልቀቂያ የአገሪቱ ጊዜያዊ መንግሥት ተቀብሎት፣ በአል ቤብላዊ መንግሥት የቤቶች ሚኒስትር ሆነው ያገለግሉ የነበሩት ኢብራሂም መህሊብ በጠቅላይ ሚኒስትርነት በመሾም ካቢኔያቸውን እንዲመሠርቱ ማክሰኞ ዕለት ተነግሯቸዋል፡፡

የአገሪቱን ትልቁን የኮንስትራክሽን ኩባንያ ከአሥር ዓመታት በላይ ሲመሩ የነበሩት መህሊብ፣ የአዲሱ ካቢኔያቸው አባላት ‹‹የቅዱስ ጦርነት ተዋጊዎች›› ይሆናሉ ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ ‹‹ፀጥታ በማስከበር ሽብርተኝነትን እንዋጋለን፤›› ያሉት መህሊብ፣ ካቢኔያቸውን በሦስት ቀን ውስጥ እንደሚያዋቅሩ ገልጸዋል፡፡ 

በሆስኒ ሙባረክ ዘመን የገዥው ፓርቲ (ናሽናል ዲሞክራቲክ ፓርቲ) አባል የነበሩት መህሊብ ካቢኔውን ሲመሠርቱ፣ አብዛኞቹን ሚኒስትሮች በነበሩበት ቦታ ላይ ይመድባሉ ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል፡፡ ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸው የሚታወቁት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሹመት በግብፅ እንደገና አመፅ ሊቀሰቀስ ይችላል እየተባለ ነው፡

ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው


ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው (Abe Tokchaw)
በዋሽንግተን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአበራሪ ሃይለ መድን አበራ ያላቸውን ድጋፍ በሰላማዊ ሰልፈ መገልፃቸው ተሰምቷል። ሰለፈኞቹ ትላንት በስዊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ተሰለፈው፤ ሃይለመድን አበራ እንደ ወንጀለኛ እንዳይታይ የስዊዝን መንግስት ተማጽነዋል።
ሰለፈኞቹ፤ አብራሪው የዘጠና ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን  ፍትህ እጦት በአለም አደባባይ ይበልጥ ያስገነዘበ ጀግና ነው ሲሉም አሞካሽተውታል።
ባልተያያዘ ዜና
ትላንት በአዲስ አባባ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ… (በቅንፍም፤ ይህ ሚሊኒየም አዳራሽ ሲገነባ ለሚሊኒየሙ ክብረ በዓል አከባበር ለስድስት ወራት ብቻ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከማን አይቶ ቦታውን ይለቃል… ይሄው ስድስት አመቱ መጣ… ሀገሪቷን ኤክስፓየርድ ዴት የማይታወቅበት ሀገር አደረጓት እኮ…ይሄው እነ እንትና ኤክስፓየርድ ካደረጉ ስንት ጊዜያቸው ገና ከአርባ እስክ ሃምሳ አመት እንፈልጋለን ይሉናል። (በሌላ ቅንፍም ሰዉ አርባቸውን ለመብላት ቋምጧል… )) ቅንፋችንን ቀናንፈን ስንወጣ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ የሚገኘው ህብረት ባንክ አጠገብ የሚስራ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ ሶሰት ጥይቶችን ወደ ሰማይ ከተኮስ በኋላ አራተኛውን በራሱ ላይ በመተኮስ ራሱን አጥፍቷል።
ሰውየው ራሱን ከማጥፋቱ በፊት ኑሮ መረረኝ እያለ ሲጮህ እንደነበር አዲሳባ የምትገኘው ጋዜጠኛ ፂዮን ግረማ ኮረጄያለሁ።
እንግዲህ ይህንንም እብድ ነው እስኪሉን ድረስ የሃገራችን ሁኔታ የገዛ አውሮፕላን የሚያስጠልፍ የገዛ ክላሻችንን የሚያስጠጣ ሆኖ ቀጥሏል። ማለት እንችላለን።
ዜናው በዚህ አለቀ!
መከራችንም በዚሁ ባለቀ!

torsdag 20. februar 2014

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በራሱ ረዳት ካፕቴን መጠለፍ የአገራችንን የአመራር ችግሮችና የሃሣብ ድህነት ክፉኛ አጋልጧል!

February 19, 2014
በክፍያለው ገብረመድኅን – The Ethiopia Observatory
የካቲት 17 በጥዋት የጠለፋውን ዜና እንደስማሁ፡ የቅድምያ ተግባሬ ያደረግሁት ለማዘጋጀው ድህረ ገጽ መረጃዎችን ማሰባስብና መረጃዎቹን መመዘን ነበር። ለዚህም ስል: ያሰባስብኩት መረጃ ምን ያህል ለእውነተኝው ሁኒታ ቅርበት አለው የሚለውን በመመዘን ጥቂት ጊዜ አሳለፍሁ።Ethiopian Airlines was absorbed by the TPLF mafia
አንዳንዶቹ ለጊዜው ትክክል ባይሆኑም፡ እንዳለ ማቅረቡ ምክንያታዊ እስከሆኑ ድረስ: ዛሬ ያለውን የመረጃ ጥማት ማርካት ብቻ ስይሆን፡ ለወደፊትም አንድ ሁኔታ በዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እንዴት ተዘገበ ለሚለው በምስክርነት ሊረዳ ይችላል።
በወቅቱ በአንድ ጊዜ፡ በተከታታይ በገጼ ላይ እንዳቀረብኩት ሁሉ፡ ብዙ የውጭ ምንጮችን ቃኝሁኝ። ጠቃሚ መረጃዎችንም አገኝሁኝ። በዚያን ወቅት አንድ ነገር ያላድረግሁት ነገር፡ መረጃ ከኢትዮጵያ ለማግኝት መሞከር ነበር። አንደኛ መረጃ ቢኖራቸውም፡ ቀዳሚው መንፈሳቸው የሚቀናው መረጃውን ማፈን ነው!
በሌላ በኩል ደግሞ፡ አውሮፕላኑ ከተጠለፈበት አገር በመጀመርያ ደረጃ መረጃ ማግኘቱ ጠቃሚነቱ ቢታወቅም፡ እንደ ኢትዮጵያ ዐይነት መረጃ መጀመርያ በባልሥልጣኖች መወሰን ባለበት ሃገር ውስጥ፡ ሲተሻሹ ጀምበር ስለሚጠልቅባቸው፡ የሃገር ውስጥ ሚዲያ ዜናውን እንዲያወራ ቢፈቀድለት እንኳ፡ እነርሱም እኛ ገና በማለዳው ያየናቸውን የሮየተርስ፡ ቢቢስ፣ ሲኤኔአንን ወዘተ ነው መልሰው የሚደጋግሙት።
ለማንኛውም፡ አቶ ረድዋን ሁሴን ወደሚዲያ ከቀረቡበት ክረፋዱ በኋላ የነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተሳከረ።
አንድኛ፡ ሥዕል ውስጥ ጠላፊው ረዳት ካፒቴን አንድ መሆኑ ቀርቶ ክአንድ በላይ የሆኑ ጠላፊዎች አውሮፕላኑ ውስጥ መግባታቸውን አስሙን።
ሁለተኛ፡ አውሮፕላኑን የጠለፊው ሰው እኔነኝ ብሎ ጠላፌው እጁን ለስዊስ መንግሥት ከሰጠ በኋል: አቶ ረድዋን ጠላፊዎቹ እያሉ በሕዝበ መገናኛ ላይ መንዛታቸውን ቀጠሉ።
ሶስተኛ፡ የዚህ ዐይነት አጣዳፊ ሁኔታ፡ በየፈጣን ደቂቃዎች የሚለዋወጡበት በመሆኑ አስቸጋሪነቱ ግልጽ ነው። ቢሆንም፡ አቶ ረድዋን የተለመደውን የመንግሥታቸውን ቀጣፊነት ባህሪ ማንጸባረቅ ስለነበረባቸው፡ ትኩረታቸው ያረፈው፣ የራሳቸው ዕውነታ (realty) ላይ ሆኖ ዜና ፈጠራ ላይ ነበሩ። ይህም እርሳቸውን እንደግለሰብ ቀባጣሪ ከማድረጉም በላይ፡ ሀገራችንን አሳፋሪ ሁነታ ላይ ጥሏታል።
በእዲህ ያለሁኒታ ውስጥ፡ ማንኛውም ባለሥልጣን ተረት ተረት (fiction) ከመፍጠር ይልቅ፡ በሠለጠነው ዓክም እንድሚደረገው፡ “ለጊዜው መረጃ የለኝም፡ እስካገኝ ጠብቁኝ” ማለቱ ያስከብራል እንጂ አያስንቅም – ባልሥልጣኑ ቃሉን ጠብቆ ያ መረጃ ካለበት ቦታ ቆፍሮ ለጠያቂዎቹ የማቅርብ ቁም ነገርኝነቱን እስካስመስከረ ድረስ!
መንግሥታቸው ለሥልጣኔ አስጊ ናቸው ብሎ የሚጠራጠራቸውን ንጹሃን “አሽባሪዎች” እንደሚላቸው ሁሉ፡ ከዚህ የአውሮፕላን ጠላፍ ጋር በተያያዘ አቶ ረድዋን ዋናዋ ተጠራጣሪ ሱዳን መሆኗን የራሳችውን ውንጀላ ሠነዘሩ።
እኔ የሱዳን ባለሥልጣን ብሆን አንድ ትልቅ የዲፕሎማቲክ የቅሬታ ማስታወሻ (demarche) ለአዲስ አበባ ሳይውል ሳይድር እንዲቀርብ አደርግ ነበር። ለማንኝውም እነዚያም እጆቻቸው ብዙም ጻዳ ባለመሆናቸው፡ ብዙም ላይረበሹ ይችሉ ይሆናል። እንዲያውም፣ የተባበሩት መንግሥታት የራሱንና የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትን ስላም አስከባሪ ሃይል ዳርፉር ውስጥ በሥውር በመውጋት ላይ የምተገኘው ራሷ ሱዳን ናት የሚለው የእሁዱ ክስ በቂ ምስክርነት ይሰጣል። (UN report points finger at Sudan over UNAMID attacks)
ሌላው አስገራሚው ነገር፡ የኢትዮጵያ ቴሊቪዥን ቅጥፈት ነው። የአውሮፕላኑ ጠላፊ ረዳት ካፒቴን “ኃይለመድህን አበራ” (ክአህራም የተገኝ) ክሲቪል አብቭዬሽን ሠራተኞች ጋር ተደጋጋሚ የአየር ላይ ግኑኝነት አድርጎ በመስኮት ወጥቼ መጣለሁ ማለቱን እየስሙና: እጁን በሰላማዊ መንገድ ለስዊስ ፖሊሶች መስጠቱ እየተስማ፡ “ሊያመልጥ ሲል ተይዞ በቁጥጥር ሥር ዋለ” በማለት ያቀረቡት ሀስት ዜ ለአንዴና ለመጭረሻ ጊዜ አገራችን ምን ያህል በወበዴዎች ቁጥጥር ሥር መሆኗን አረጋግጦልኛል።
ይህ ደግሞ የሚመነጨው – በቅርቡ በረከት ስምኦን እንዳለው – ከሕዝብ ንቀት ነው። የፈለግነውን ብንቀባጥርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ያምነናል ከሚል የዋህ አስተሳሰብ ነው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ራስቸውን ብቻ ነው ያዋረዱት!
በራሱ ካፕቴን የተጠለፈው አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በራሱ ረዳት ካፕቴን መጠለፍ፡ በዓለም ታሪከ ውስጥ ውሱንና ጥቂት ተጠቃሽ ምሳሌዎች ያሉት ውርደት ነው። በባለሙያ ደረጃ ግለስቡ ደህና ደሞዝ ያገኛል (በአንጻራዊ ደረጃ ከኅብረተስቡ ጋር ሲወዳደር – ከሕወሃት ባልሥላጥኖችና ካድሬዎች ጋር ባይሆንም)። ስለዚህ ይህ ሰው የኢኮኖሚ ጉዳይ ነው እንዲሰደድ ወይንም አውሮፕላን ጠልፎ ስደት እንዲጠይቅ ያስገደደው ለማለት አይቻልም።
ይህ ሁኔታ ደግሞ አገራችንን ወደተጠናወታት፡ የመብት ረገጣና የስብአዊ መብቶች ገፈፋ እያመለከተ ነው። ጤንነቱን መጠራጥር አይቻልም – የመንግሥት የፕሮፓጋንዳው ሹም፡ ፓይለቱ የወንጀል ሪኮርድ የለበትም፡ ጤንነቱንም በተለመከተ “was medically sane until otherwise proven” ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ስኞ ከቀትር በኋላ ዘግቦታል
ይህ ደግሞ ወደዋነኛው ሀቅ ይመልስናል – ይህም የኢትዮጵያ ችግር የመንግሥትና የአስተዳደር እንጂ፡ ሌላ እንዳልሆነ ነው!
በሕወሃት አመራር ወዳዘቅቱ
የኢትዮጵያ ችግር ከቀን ወደቀን እየከፋ የመጣው በዘረኛው መንግሥት ፓሊሲዎች ምክንያት ነው። ሲሻው አማራ፡ ኦሮሞ፡ ሶማሌ … ብሎ ከፋፍሎ ሊያባላን የተነሳ መንግስት ነው ያለን። በቅርቡ ሆድ አደር አዝማሪ በፓለቲካ አመራር አማክይነት በብአዴን ድሕፈት ቤት ሃላፊ የተሰነዘረው – በዓለም አቀፍ ሕግ በሰው ዘር ላይ የተፈጸመ ወንጅል ተደርጎ የሚወስደው – ጸረ አማራ ወራዳ የስድብ ጋጋታ ሥርዐቱ ከነሥረ መሠርቱ ያለውን ብልሹነትና ወንጀልኝነት የሚያሳይ ነው።
ባልሥልጣኖቹ ይህን ባስተጋቡ መጠን ተለክቶ የፓሊቲካ ጽዋቸው ይሠፈራል! መዘንጋት የሌለበት፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ዓመት በስመ ኦሮሞ ነጻ አውጭ ውንጀላ ፓርላማ ውስጥ ያስሙት/ያሰማው ጸረ-ኦሮሞ አነጋገር፡ በዘፈቀደ የመጣ አይደለም – ሕወሃት ሀገራችን ውስጥ የዘራው ቫይረስ ውጤት ነው!
በቅርቡ የአገሪቱን ዳር ድንበር በመሽረፍ ለሱዳን የአርሻ መሬት ለመስጠት የተደረገው ምሥጢራዊ ስምምነት፡ ለኢትዮጵያም ሆነ ለሕወሃት ትልቅ የጥፋት ምንጭ ይሆናል። ጸጥ በለው ክርመው፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡ ስሞኑን ይህንን ለማስተባበል ሞክሩ። ሆኖም፡ ሃይማኖተኛ ነኝ የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ሥልጣን ከያዙበት ጊዜ ጅምረው ባሉት 18 ወራት ግን ሃይማኖታቸው ሃስት መናገርን ሲከለክላቸው አልተመለክትንም።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሸርሸር
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኩራታቸን ክሆነባቸው ምክንያቶች አንዱ የፓይለቶቻችንና የመካኒኮቻችን ብቃት፡ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የኩባንያውያን ኢትዮጵያውያንነት ለማሳደግና ለማበልጸግ ማስቻሉ ነበር።
ዛሬ ግን ኢትዮጵያዊ ፓይለቶች በዘር ልዩነት ምክንያት እየተገፉ፡ የሚወዱትን ኩባንያ እየተዉ ወደመካከለኛው ምሥራቅና በየአህጉሩ እይተበተኑ ናቸው። ዛሬ በጣሊያን አብራሪ የሚመራው አውሮፕላን – ኢትዮጵያዊ ሳይሆን – መጠለፍ፡ በዘረኛው ሕወሃት መዳፍ ሥር አገራችን በየፊናው የምታመራበትን አዘቅት የሚያመላክት ነው!
ኢትዮጵያውያን ለአገራችን ቀናተኞች ነን- አገርን አሳልፎ መሽጥ ባህላችን አይደለም። አልጨበጥ ባይነት፡ ቀባጣሪነትነና በዜጎች ጉስቅልና ላይ የፕሮፓጋንዳ ድራማ መሥራት (ሳኡዲ በነበሩት ላይ እንደተፈጸምው ሁሉ)፡ ኃይልን ተገን አድርጎ መክናፈስ ፍጻሜው መጥፎ ነው – ታሪክ እንደሚያሳየን!
ታዲያ በጥቂቶች ጠባቦችና የሥልጣን ባለጌዎች መጥፎነት ለምን መላው ሃገር ይታመሳል? ህገርስ ዐይናችን እያየ ለምን አገር ወደአዘቅት ታምራ?
ይህንን የመገንዘቡ አዝማሚያ በማይታይበት በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዴት ነው ዜጎች በየቀኑ እየተገፉ እየተረገጡ ሊቀጥሉ የሚችሉት? በመንግሥት ሥልጣን ላይ መንግሥታዊ ባህሪ የሌላቸው ስዎች በመቀመጣችው፡ የባሱ ዜጎችን የሚያሽማቅቁ፡ አገር ሊያውርዱ የሚችሉ፡ ትውልድን የሚያሳፍሩ ገና ብዙ ነግሮች ሊመጡ ይችላሉ – በመንግሥት ላይ የሠፈሩት ሆድ አደሮች ቆም ብለው ከአሁኑ አሳፋሪ ነገር አንዳችም መማር ካልቻሉ።
በነገራችን ላይ፡ ገና ከማለዳው አውሮፕላኑ እንደተጠለፈ የብዙዎቹ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ገለጻ: ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የስብአዊ መብቶች ላይ ማተኮራቻው በቂ ምልክት ተደርጎ ሊወስድ ይገባል!

mandag 10. februar 2014

የአቶ አሥራት ጣሴ እስር የኢህአዴግ የጉልበት ፖለቲካ ማሳያ ነው!

February 10/2014

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የተሠጠ መግለጫ

ፓርቲያችን አንድነት በተደጋጋሚ ከገዥው ፓርቲ ህግን ከለላ በማድረግ እና የመንግስትን ሥልጣን በመጠቀም የሚደርስበትን ከፍተኛ አፈና ተቋቁሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ ትግሉን አጠናክሮ መቀጠሉ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡
በተለይም ፓርቲያችን በመላው የሀገራችን ክፍል የዘረጋውን መዋቅር በህዝባዊ አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ በማሸጋገር በአምስት ዓመት ስትራተጂክ ዕቅዱ መሰረት እያከናወነ ያለው ህዝባዊ ንቅናቄ እና በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባዔ አካሂዶ ዴሞክራሲያዊ የአመራር ሽግግር ማድረጉ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ያሳደረ ቢሆንም ገዥውን ፓርቲ በአንጻሩ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደከተተው ይስተዋላል፡፡
ኢህአዴግ ቀደም ሲል የፓርቲያችንን እንቅስቃሴ በመከታተል ከከፍተኛ አመራሮች መካከል አቶ አንዱዓለም አራጌ፤ ናትናዔል መኮንን እና ሌሎች በርካታ አባላትን የተለያየ ምክንያት ፈጥሮ እየወነጀለ ለእስር መዳረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህም በድንገት የተደረገ ሳይሆን የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና የኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ መለስ ዜናዊ በግልጽ በፓርላማ ተገኝተው ‹‹አንድነት ፓርቲ እግር ሲያወጣ እግሩን እንቆርጣለን›› ባሉት መሰረት የፈጸሙት ነበር፡፡
አሁንም የራዕያቸው አስቀጣይ ነን የሚሉ የገዥው ኃይሎች ፈለጋቸውን ተከትለው የአውራ ፓርቲ (የአንድ ፓርቲ ስርዓት) ለመገንባት አንድነትን በጉልበት ፖለቲካ ማጥፋት እንደ ብቸኛ መንገድ ወስደው እየተረባረቡ ይገኛሉ፡፡ በመላው የሀገራችን ክፍል በርካታ አባሎቻችን ከስራ ተፈናቅለዋል፤ በግፍ ከሀገራቸው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፤ ታስረዋል፤ ተደብድበዋል፡፡ ይህም በየጊዜው በፓርቲያችን ልሳን በመረጃ ተደግፎ ለህዝብ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በፓርቲያችን አመራር እና አባላት ላይ የተፈጸመውን የሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ባመላከትንበት ሪፖርትም ተካተቶ ለህዝብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በተለይም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል የተካሄደውን ህዝባዊ ንቅናቄ ተከትሎ ፓርቲያችን በተንቀሳቀሰባቸው አሥራ አንድ የሀገራችን ከተሞች ጉልህ ሚና የተጫወቱ እና በህዝብ ተቀባይነት ያላቸውን አባላት ምክንያት እየፈጠሩ እና የፍትህ ስርዓቱን የፖለቲካ መሳሪያ እያደረጉ ለእስር እና ለእንግልት መዳረጉን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡
ኢህአዴግ ገና በጊዜ የጀመረው የ2007 ዓ.ም የምርጫ ዘመቻ የተለመደውን የጉልበት ፖለቲካ የተከተለ ሲሆን በቅርቡ በምዕራብ ሸዋ ዞን ለንሴቦ ወረዳ አቶ አለማየሁ ለሬቦ የተባሉ የሲተዳማ ዞን የአንድነት ስራ አስፈጻሚ በአዲስ አበባ ተገኝተው የፓርቲ ጉባኤ ተሳትፈው ሲመለሱ በቁጥጥር ስር ውለው ለ22 ቀናት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በእስር ቤት ከተሰቃዩ በኋላ መንግስትን ሰድበዋል የሚል ክስ ተመስርቶባቸው በዋስ ተለቀዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ በየካቲት 30 ቀን የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራር (የብሄራዊ ምክር ቤት አባል) የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ ፍርድ ቤትን ዘልፈዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉ ሲሆን ሌሎች አራት ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች ሊታሰሩ ሴራ እየተሸረበባቸው መሆኑን ምንጮች ለፓርቲያችን እያረጋገጡ ይገኛሉ፡፡
የፍትህ ስርዓቱን ዋነኛ የፖለቲካ መሳሪያ ያደረገው የኢህአዴግ መንግስት አቶ አስራት ጣሴን ለማሰር እንደ ምክንያት የተጠቀመው በአዲስ ጉዳይ መጽሄት 197 ቅፅ 7 ያወጡትን ጽሑፍ ሲሆን አጠቃላይ መልዕክቱም በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ የሌለ መሆኑን፤ ህጎች አፋኝ መሆናቸውን፤ ኢ.ቲቪ የሰራቸው አኬልዳማ፤ ጀሃዳዊ ሃረካትና ሌሎች ለፖለቲካ ጥቃት ማድረሻ የተቀነባበሩ ድራማዎች ህገ ወጥ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ይህ የፍትህ ጥያቄ ደግሞ አቶ አስራት ጣሴ ገና በጠዋት ለትግል የወጡበት፤ ከመሰሎቻቸው ጋር ሆነው አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍት ፓርቲ እንዲመሰረት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉበት የፖለቲካ አላማቸው እና የፓርቲ አቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡
‹‹የኢህአዴግ መንግስት ከሚመራቸው ፍርድ ቤቶች ፍትህ ይገኛል ብለን ሳይሆን ለታሪክ እንዲመዘገብ ወደ ፍርድ ቤት እንሄዳለን›› ሲሉም የግል ሃሳባቸው ብቻ ሳይሆን በብዙ አንቀጽ የተጠቀሰ የፓርቲያቸው አቋም ስለመሆኑም ማሳያ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ኪሊማንጃሮ የተባለው ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በመንግስት ተቋማት ላይ ያደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት መካከል ፍርድ ቤቶች በአንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ናቸው፡፡
ከነዚህ በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት ፍትህ አይገኝም ብሎ ማመን እና እምነትን መንገርም ሆነ መጻፍ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑ እየታወቀ በአካል ባልተገኙበት ችሎት በአካል ተገኝቶ ችሎትን ያወከ ወይም የዘለፈ በሚቀጣበት ፍታብሔር አንቀጽ 480 ቀርበው እንዲያስረዱ ከተጠሩ በኋላ ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ የተጠሩበት የፍታብሔር አንቀጽ የሚያዘው ጥፋታኛ ሆነው የተገኙ ቢሆን እንኳ በአነስተኛ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ እንጂ ለእስር የሚያበቃ አልነበረም፡፡
ኢህአዴግ ይህንን እያደረገ ያለው ቀናቶች ወደ 2007 ዓ.ም ምርጫ እየገሰገሱ እና ፓርቲያችንም በህዝባዊ አቅሙ እየጎለበተ በመምጣቱ ካለቃቸው እንደተማሩት እግር ያወጣ ፓርቲያችንን እግር በመቁረጥ፤ አመራሩን ህግን ከለላ አድርገው ለእስር በመዳረግ፤ እንዳይጽፍ፤ እንዳይነገር እና በፍርሃት ቆፈን ተይዞ አንገቱን እንዲደፋ በማድረግ በምርጫ ሜዳው ከጀሌዎቻቸው ጋር ሩጠው አሸንፈናል ብሎ ለማወጅ የሚደረግ አስነዋሪ ዘመቻ ነው፡፡
ነገር ግን እንዲህ ያለው አምባገነናዊ ተግባር ትግላችንን የበለጠ አጠናክረን በመግፋት ሰላማዊ ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋዕትነት ለመክፈል የሚያበረታን እንጂ ወደኋላ የማይመልሰን መሆኑን ዛሬም እንደ ትላንቱ ለመላው ህዝባችን እናረጋግጣለን፡፡
የፍትህ ስርዓቱም ከአንድ ፓርቲ ወገንተኝነት እንዲወጣ እና በግፍ የታሰሩ አመራሮቻችንንም በነጻ እንዲያሰናብት እንጠይቃለን !!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

የካቲት 1 ቀን 2006ዓ.ም

fredag 7. februar 2014

የአንዷለም አራጌ የውሳኔ አሁንም ቀጠሮ ተራዘመ፤ ኢሕአዴግ 4 የአንድነት አመራሮችን ሊያስር መሆኑ ተሰማ

February 7/2014

ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያውያን ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሰው በሚል የተሰየመው ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ በካንጋሮው ፍርድ ቤት ዕድሜ ልክ ዕስራት እየተፈርደበት መሆኑ ይታወሳል። ወጣቱ ፖለቲከኛ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን ለውሳኔ ከተቀጠረ በኋላ አሁንም እንደዚህ ቀደሙ ቀጠሮው መራዘሙን የዜና ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ጠቁመዋል።

አቶ አንዷለም አራጌ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ወህኒ እየተሰቃየ ቢሆንም “የእኔን መታሰር ተቃዋሚዎች ሊጠቀሙበት አልቻሉም” ሲል መናገሩ አይዘነጋም። ዛሬ ፍርድ ቤት መቅረብ የነበረበት አንዷለም በዳኞች የተለመደ ምክንያት ቀጠሮው ለመጋቢት 8 ቀን 2006 እንዲተላለፍ ተወስኗል። ዛሬ አንዷለም ላይ ምን ይወሰን ይሆን የሚለውን ለማየት በርካታ ሰዎች ስድስት ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታድመው እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመልከታል።

የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘጋቢ ነብዩ ሃይሉ እንደዘገበው ኢህአዴግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ አራት የአንድነት አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ተጋለጠ። በዘገባው መሠረት ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ 4 አመራሮችና አባላት እንዲታሰሩ ኢህአዴግ ወስኗል፤ የክስ ቅድመሁኔታዎች በፍርድ ቤት መጠናቀቃቸውን ታውቋል፡፡


የፍትህ ሚ/ር ምንጮች እንዳስታወቁት በኢህአዴግ ጽ/ቤት ትዕዛዝ ክስ እንዲከፈትባቸውና እንዲታሰሩ የተወሰኑት የአንድነት አባላት በርካታ ናቸው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ዙር ክስና እስር በ4 አመራሮችና አባላት ላይ ያነጣጠረ ነው ይላል የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘገባ።

አቶ አስራት ጣሤ ታሰሩ

አቶ አስራት ጣሤ ታሰሩ

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ፣ በክስ ሂደት ላይ የነበረው የአኬልዳማ ዶክመንተሪ በድጋሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መታየቱን ተከትሎ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ከፃፉት አስተያየት ጋር በተያያዘ “ዘለፋ አዘል ጽሑፍ” ጽፈዋል በሚል ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ በተላለፈባቸው መሰረት በዛሬው እለት በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የተገኙ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለ7 ቀን ታስረው በቀጣዩ ሳምንት እንዲቀርቡ በማለት የእስር ትዕዛዝ ወስኖባቸዋል ፡
ኢህአዴግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ አራት የአንድነት አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ተጋለጠ::
ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ 4 አመራሮችና አባላት እንዲታሰሩ ኢህአዴግ ወስኗል፤ የክስ ቅድመሁኔታዎች በፍርድ ቤት መጠናቀቃቸውን ታውቋል፡፡
ኢህአዴግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ አራት የአንድነት አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱን የፍትህ ሚ/ር ምንጮች አጋለጡ፡፡ ምንጮቹ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት በኢህአዴግ ጽ/ቤት ትዕዛዝ ክስ እንዲከፈትባቸውና እንዲታሰሩ የተወሰኑት የአንድነት አባላት በርካታ ናቸው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ዙር ክስና እስር በ4 አመራሮችና አባላት ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡

lørdag 1. februar 2014

የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከሃገር ፈረጠጡ

February 1/2014


(ዘ-ሐበሻ) ራሳቸው በጠሩት ግምገማ፣ ራሳቸውን አስገምግመው ከፓርቲው ሊቀመንበርነታቸው መነሳታቸው የንጽህናቸው ውጤት መሆኑን ሲናገሩ እንደነበረ የሚነገርላቸውና በአንድ ወቅት በጋምቤላ ስለነበረው ጭፍጨፋ ተጠያቂ ነህ ሲባሉ “መሳሪያውን ያቀበለው መለስ ዜናዊም መጠየቅ አለበት” ብለዋል የተባሉት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንትና የአሁኑ የፌዴል ጉዳዮች ሚ/ር ደኤታ አቶ ኦሞት ኦባንግ ከሃገር መፈርጠጣቸው ተሰማ።

በስልጣን ዘመናቸው ፕሬዚዳንቱ የክልሉን ደን እያስጨፈጨፈና ህዝቡን እያፈናቀለ ስላለው የመሬት ሽያጭና ነጠቃ የክልሉ እጅ የለበትም በሚል የተናገሩት ኦሞት ሂይውማን ራይትስ ዎች ባወጣው ሪፖርት ላይ በክልሉ ስለሚካሄደው የመሬት ነጠቃ አቶ በረከት ስምኦን በበኩላቸው ምላሽ ሲሰጡ በክልሉ ከሶስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ ባለቤት የሌለው መሬት መኖሩን መናገራቸው አይዘነጋም።
ኦሞት ኦባንግ ከሃገር እንዳይወጡ ከፍተኛ የሆነ ጥበቃ ሲደረግባቸው እንደነበር የሚታወስ ሲሆን በተለይም በጋምቤላ ክልል ስለተፈጸሙት የጅምላ ጭፍጨፋዎች በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ምስክር ይሆናሉ በሚል ፍራቻ በሕወሓት/ኢሕአዴጎች ከሃገር እንዳይወጡ ይፈራ እንደነበርና የፌደራል ጉዳዮች ሚ/ር ደኤታ የተደረጉትም “ጠላትህን አታርቀው፤ አቅርበውና እንስቅቃሴውን ተከታተለው” በሚለው የፖለቲካ አካሄድ እንደነበር የውስጥ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ይህን በማስመልከትም አዲሲቷ ኢትዮጵያ ለጋራ ንቅናቄ በአንድ ወቅት ባወጣው መረጃ “አቶ ኦሞት ካገር ከወጡ አቶ መለስና መንግስታቸው ላይ ምስክር ይሆናሉ። አቶ ኦሞት ከተሰደዱ በአካል ለዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምስክርነታቸውን መስጠት ግዳጃቸው በመሆኑ የህወሃት ሰዎች ስጋት አለባቸው። ስለዚህ አቶ ኦሞት በተቀመጠላቸው የስድስት ወር የሃላፊነት ዘመናቸው አድርጉ የተባሉትን እየፈጸሙ ይኖራሉ። የህወሃት ሂሳብ ይህ ቢሆንም በመጨረሻ ያልታሰበ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል እገምታለሁ። ምክንያቱም ነገሮች ተነካክተዋል” የሚል አስተያየት አስነብቦ እንደነበር ይታወሳል።

የሚኒስትር ዲኤታውን ኩብለላ በተመለከተ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተጠየቁት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም አቶ ኡመt በስራ ገበታቸው ላይ እንደሌሉ ማረጋገጣቸውን ገልጸው መስሪያ ቤታቸው ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝ ሲናገሩ አቶ ኡመትም ወደ ሃገራቸው መመለስ እንደማይፈልጉ መናገራቸውን ጨምሮ የመጣው መረጃ ሲጠቁም፤ አሁን ግን የት ሃገር እንዳሉ ለጊዜው ማረጋገጥ እንዳልተቻለ ተጠቁሟል።

በጋምቤላ በተፈፀመው ጭፍጨፋ የሚከተሉት ሰዎች በዋነኝነት ለፍርድ መቅረብ አለባቸው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።

1. አባይ ፀሀዬ (በጊዜው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር የነበረ)
2. ዶ/ር ገብረአብ ባርናባስ (በጊዜው ሚኒስትር ደኤታ የነበረና በቦታው በመገኘት ጭፍጨፋውን ያስተባብር የነበረ)
3. ኮለኔል ፀጋዬ (በጊዜው በቦታው የነበረው ወታደራዊ ሀይል አዛዥ)
4. ኡመት ኦባንግ (አሁን ከሃገር የፈረጠጡት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል አስተዳዳሪ)።