onsdag 24. desember 2014

በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ

∙ተከሳሾቹ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል
∙‹‹ለማን አቤት ይባላል?›› ሀብታሙ አያሌው
በላይ ማናዬ
ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተሟልተው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል፡፡
ችሎቱ የተሰየመው ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ወቅት ተከሳሾች በቀረበባቸው የሽብር ክስ ላይ የሰጡትን መልስ በተመለከተ 7ኛ ተከሳሽ መልስ በዕለቱ ባለማቅረባቸው አሟልተው እንዲቀርቡ ነበር፡፡ በተጨማሪም ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ስለነበር ይህን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ በታዘዘው መሰረት ማብራሪያውን ለመስማት ነበር፡፡
የተከሳሾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በጥየቃ ወቅት በተለየ መዝገብ ይመዘገባሉ የተባለውን አቤቱታ በተመለከተ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በደብዳቤ መልስ መስጠቱ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ‹‹ማረሚያ ቤቱ በሰጠው መልስ እስረኞች ከሌሎች በተለየ የደረሰባቸው ችግር የለም›› ማለቱን ገልጾ ይህንኑ መልስ ሙሉ ለሙሉ መቀበሉን አስታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በዛሬው የችሎቱ ውሎ ላይ ተከሳሾች ለየት ያለ አቤቱታ በጠበቆቻቸው በኩል አቅርበዋል፡፡ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለችሎቱ እንዳስረዱት ደንበኞቻቸው ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ አቶ ተማም አባቡልጉ በታህሳስ 12 ለ13 ቀን 2007 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት ስምንት ሰዓት ጀምሮ ደንበኞቻቸው ላይ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የግል ማስታወሻዎቻቸው፣ ገንዘብ እና በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ እያዘጋጁት የነበረው መቃወሚያና መከራከሪያ ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡
‹‹ደንበኞቼ ላይ እየተደረገ ያለው ጉዳይ ለህይወታቸውም የሚያሰጋቸው ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ በሌሊት ፍተሻ ያደረጉባቸው ሰዎች ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ‹ህገ-ወጥ› ተግባራት ሲፈጽሙባቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስና የደህንነት አባላት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ደንበኞቼ ያውቋቸዋል፡፡ ስለሆነም ፍተሻው የተከናወነው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አልነበረም ማለት ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው የተለየ የስም ዝርዝር ተይዞ ከሌሎች በተለየ መልኩ ነው፡፡ ለአብነት ደንበኞቼ አቶ አብርሃ ደስታና በሌላ የክስ መዝገብ የተከሰሰው አብዱራዛቅ አክመድ ላይ የሆነው ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ነው፡፡ ፍተሻው ስለት ነገር አልያም ሌላ ህገ-ወጥ ቁሳቁስ ለመያዝ የተደረገ አለመሆኑን ከተወሰዱት ንብረቶች ማየት ይቻላል›› ሲሉ አቶ ተማም ለፍርድ ቤቱ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመውን ድርጊት አስረድተዋል፡፡
ይህን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ ‹‹ማረሚያ ቤቱ መንግስት ዜጎች ታንጸው እንዲወጡ ያሰራው ነው፡፡ ይህን አሰራር ለመጠበቅም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የተለያዩ ስራዎችን ሊሰራ ይችላል፡፡ እየቀረበ ያለው አቤቱታም ከዚህ አኳያ መታየት ያለበት ነው›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ከህግ አንጻር ያስረዱ ሲሆን፣ ‹‹በመሰረቱ ፍተሻ ሊካሄድ መቻሉ ላይ አይደለም አቤቱታው፡፡ የተካሄደው ፍተሻ ግን ህገ-ወጥ ነው፤ ምክንያቱም ፍተሻው የተከናወነበት ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ባለው ጊዜ ሳይሆን ሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ፍተሻው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አይደለም የተከናወነው፡፡ በደህንነቶችና የፌደራል ፖሊሶች ነው ፍተሻው የተደረገው፡፡ ይህም ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎቱም ሆነ ብቃቱ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ ይህን መሰል ድርጊት የፈጸሙት አካላትና በማን ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ምርመራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም በተጨማሪ ከደንበኞቻቸው ላይ በፍተሻው ወቅት የተወሰዱባቸው ንብረቶችና ማስታወሻዎች እንዲመለሱላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ‹‹የተለየ ከፍተኛ በደል ደርሶብኛል›› በሚል ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ዕድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው የነበሩት 3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ የጠየቁት የመናገር እድል ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡
በጠበቆቹ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታን በተመለከተ ችሎቱ አስተያየት የሰጠ ሲሆን በተለይ ጠበቃ ተማም አቤቱታውን ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎትም ብቃትም የለውም›› ያሉት አገላለጽ ተገቢ ስላልሆነ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በቃል የገለጹት የመሐል ዳኛው፣ ‹‹እንዲህ አይነት አገላለጽ ማረሚያ ቤቱ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ እንዳይሆን…›› በማለት ሌላ አስገራሚ መነጋገሪያ ከፍተዋል፡፡
ይህን የዳኛውን ንግግር ተከትሎ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የመናገር እድል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ ለአጭር ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ እናም፣ ‹‹እርስዎ እያሉት ያለው ነገር ተገቢ አይደለም፡፡ በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይህንን ስጋቴን ለችሎት እያስረዳሁ ነው፡፡ ግን እርስዎ ‹የበቀል እርምጃ› እንዲወሰድብን ማሳሰቢያ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ በእርግጥ አሁንም የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድብን ማረጋገጫ የለንም፡፡ እሺ ለማን አቤት ይባላል? የደረሰብንን በደል ለፍርድ ቤት ከማስረዳት ውጭ ለማን አቤት እንላለን….አሁን እኮ ፍርድ ቤቱ ከማረሚያ ቤቱ ጋር መወገኑን ነው እያየን ያለነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የእኛን አቤቱታ እየሰማ አይደለም፡፡ ከፍርድ ቤት ውጭ ለማን አቤት እንበል?›› ሲል አቤቱታውን በስሜት ውስጥ ሆኖ አስረድቷል፡፡
የሀብታሙን ንግግር አዳምጠው አንደኛ ዳኛ ‹‹እኛ ሳንሆን ህጉ ነው ይህን እንድንል የሚያደርገን›› በማለት አጭር መልስ ሰጥተዋል፡፡
በዚህ መልኩ ቀጥሎ የዋለው ችሎት በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የማየት ስልጣን አለው ወይስ የለውም በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት፣ እና መደበኛ ክሱን ለማየት ለታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተጥቷል፡፡

mandag 22. desember 2014

የወደፊቱ የተሻለ የህይወት ተስፋ ያለው ወያኔ መቃብር ላይ ነው!!

ግንቦት 7
ወያኔ በሀገራችን የዘረጋው ማህበራዊ ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ ስርአት ለጠቅላላ ህዝባችን፣ በተለይ ለወደፊቱ ሀገር ተረካቢ ወጣት ሲኦል መሆኑ ቅጥሏል። በሀገሬ ውስጥ፣ ሰርቸ የተሻለ ህይወት እኖራለሁ ብሎ ማለም ቅዠት ሆኗል። ከዚህ ይልቅ ያብዛኛውን ወጣት ተስፋ ሀገር ጥሎ በገፍ መሰደድ ከሆነ ውሎ አድሯል።
በእጅጉ በሚዘገንን ሁኔታ በግፍ ተሰቃይተው ከሳውዲ አረቢያ ወደሀገራቸው ከተመለሱት ከ160 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ግማሽ ያህሉ ተመልሰው መሰደዳቸውን በቅርቡ የወጣ ጥናት አረጋግጦል። በዚህ ሁኔታ ከተሰደዱ ወገኖቻችን ውስጥ ቁጥራቸው ከ70 በላይ የሚሆኑት ቀይ ባህር ላይ የነበሩበት ጀልባ ሰምጦ አልቀዋል። እነዚህ ወገኖቻችን ጉዞቸው በሞትና ህይወት መሃል መሆኑን አስቀድመው ያውቃሉ። ይህንን ያስመረጣቸው ግን የወያኔ ስርአት ነው። የወያኔ ስርአት የተመቻቸው ለስርአቱ ሹመኞችና ለዘመድ አዝማድ ከዚያ ከተረፈ ለጎሳ ተወላጆቻቸው ብቻ ነው። ሀገሪቱ ውስጥ ተገኘ የሚባል የኢኮኖሚ እድገት ካለም ከዚሁ ከጠባብ ቡድን ጥቅም አልፎ መከረኛውን ህዝብ የሚጠግን አልሆነም።
የኢትዮጵያ ወጣቶች ከተስፋ ቆራጪነትና ሞትና ህይወትን ከሚያስመርጥ አስከፊ ህይወት ያለፈ ምርጫ አለ። ዋናው ምርጫቸውም ይህ ሊሆን ይገባል፤ ምርጫው ለዚህ መከራና ሀዘን ውርደት የዳረገንን ጨካኝ የወያኔ ስርአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ ነው።
ወያኔ የህዝቡ ጉስቁልናና ስቃይ ጉዳዩ አለመሆኑን ባለፉት ሳምንታት ከ70 በላይ ወገኖቻችን ቀይ ባህር ውስጥ ሰምጠው: አለም በሀዘን በሚመለከተንና መንግስት አለ ብሎ የሀዘን መግለጫ በሚልክበት ሰአት የብሄረሰብ ቀን በሚባል የቦልት በአል የወያኔ ሹሞች ብዙ ሚሊዮን ብር አውጥተው በውስኪ እየተራጩ ይጨፍሩ ነበር።
ይህ አልበቃ ብሎ አሻንጉሊቱ ሃይለማርያም ደሳለኝ በስደተኛው ላይ ለሰሚ የሚቀፍ የወረደ አሉባልታና ስድብ ሲያወርድ ሰምተናል፣ ራሱን ያወረደ ተረት ተረትም ተናገረ። በሥልጣን የመባለግ ዝንባሌያቸው ሳይውል ሳያድር በሚጠቀሙት የባለገ አዋራጅ ቃላት የመጠቀም ርሃባቸው አሳየን።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፦ በምድረ ኢትዮጵያ የተስፋ መቁረጥና ለወያኔ ሎሌዎቹ መሳለቂያ እንድንሆን ያበቃን ይህ የነቀዘ ዘራፊ የወያኔ ስርአት ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ስቃይና ውርደት የሚቆመው ወያኔ ሲወገድ ብቻ መሆኑን ሁላችንም ጠንቅቀን ልንረዳ ይገባል። በቅርቡ ዱላውንና ግፉን ሁሉ ለመቀበል ቆርጠው ወያኔን ከተጋፈጡት የሰማያዊ ፓርቲ አባልና ደጋፊ ወጣቶች ብዙ ልንማር ይገባል። እንደእባብ በጭካኔ መቀጥቀጣቸው አጠነከራቸው እንጂ አላዳከማቸውም።
ወያኔ ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ነቅዞል። የጭካኔውና የፍርሀቱ ምንጪ ጣር ሞቱ እንጂ ሌላ አይደለም።
ሞትና ህይወትን ከሚያማርጥ ስደት የደረሰው ወጣቱ አርበኝነትን መምረጥ አለበት። ከቀን ጅቦች ራስን በማዳን ውርደትን፣ ስደትን ማስወገድ ይቻላል። ይህ የነገ ሳይሆን የዛሬ ውሳኔ መሆን ይኖርበታል።
በመሆኑም ግንቦት 7 ወጣቱ በያለህበት በራስህ አነሳሽነት እንድትደራጅ ያበረታታል። አመች ሁኔታ ያለህ ወጣት ደግሞ ተቀላቀለን። ሰራዊቱ ውስጥ ያለህ ወጣትና ሎሌነት የሰለቸህ ሁሉ የነጻነት ሀይሎችን ትቀላቀል ዘንድ ጥሪያችን ይድረስህ።
የሀገራችን የህዝባችንና የያንዳንዳችን የተሻለ ህይወትና ዘመን ተስፋ የተቀመጠው ወያኔ መቃብር ላይ መሆኑን መዘንጋት የለብንም።
ድል ኢትዮጵያ ህዝብ!!!
source www.ginbot7.org

በምርጫ ቦርድ ደባ አንድነት አይደናገጥም! ሲል አንድነት ፓርቲ መግለጫ ሰጠ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍና ለዚህም መተማመኛው ሕዝቡ መሆኑን ገልፀ «ተደራጅ 2007 ለለውጥ» በሚል መፈክር አንግቦ አገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና ኢህአዴግን በቃህ ለማለት ሌት፣ ከቀን በንቃትና በትጋት እየሠራ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት ነፃ ሚዲያ በታፈነበትና በተዘጋበት አንድነት የራሱን የማተሚያ ማሽን ገዝቶ በየጊዜው ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ በሚጠፋው የኤሌክትሪክ ችግርን ለማሸነፍ የራሱን ከፍተኛ ኃይል ያለው ጀነሬተር በመግዛት በሣምንት የራሱን ጋዜጦችን እያተመ እያንዲያሰራጭ ተገዷል። ምሁራን፣ ወጣቶች፣ ጋዜጠኞችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለወሳኑ የ2007 ምርጫ ትግል እየተቀላቀሉት ይገኛሉ። አንድነት በአሁኑ ሰዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉን በአግባቡ ለመምራትና ለውጥ ለማምጣት በተሻለ ቆመና ላይ ነው ያለው።
በምርጫ ቦርድ በአንድት ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ሆነ በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ የሌለውን የጠቅላላ ጉባኤ አባላትና የምላተ-ጉባኤ ቁጥር በተሻሻለው ደንባችን ውስጥ እንድናካትት የተወሰነብንን ፈርድ ገምድል ድርጊት ሕገ-ወጥ መሆኑን ብናውቀውም ጠቅላላ ጉባኤ መጠራትን እንደ ጉዳት ሳይሆን አንደ ልዩ እድል በመቁጠር፣ 320 የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በመጥራት የምርጫ ቦርድ ተወካይ በተገኘበት የተሳካና አንፀባራቂ ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደናል። የጠቅላላ ጉባኤውንም ሰነድ ታህሣሥ 10 ቀን 2007 ዓ.ም ለምርጫ ቦርድ ገቢ ተደርጓል።
ሁሉ እንደሚገነዘበው በአሁኑ ሰዓት ሕዝቡ በኑሮ ውድነትና በሥራ እጦት ከመሰቃየቱም በላይ ሙስና ሰፍኗል፤ መልካም አስተዳደር የሕግ የበላይነት ከቶውንም ጠፍቷል። የሕዝብ የነፃነትና የዴሞክራሲ ጥያቄ ገዝፎና አፍጥጦ እየመጣ ነው። በመሆኑም ኢህአዴግ በፍርሃትና በጭንቀት እየራደ ነው። ምረጡኝ ብሎ ሕዝብ ፊት ለመቅረብ የሚያስችለው የፖለቲካና የሞራል ኃይል ስለሌለው ውሸት፣ ማስፈራራት ማሰር መግደል ማሸነፊያ መሣሪያዎች እንዳልሆኑትም በግልጽና በትክክል ተደራጅቷል። አሁን የቀረው ማሸነፊያው መንገድ አንድነት ፓርቲን በመዝጋት ነው የሚል ድምዳሜ ላይ በመድረሱ ጥንቱንም የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች የሆነውን ወኪሉን በመጠቀም በአንድነት ላይ ዘመቻ ከፍቷል።
ታህሣሥ 10 ቀን 2007 ዓ.ም በምርጫ ቦርድ ከፍተኛ አመራር የተሰጠው በቅጥፈትና በውሸት የተሞላው መግለጫም የሚያሳየውና የሚመሰክረው ይህንኑ ነው። ነገር ግን እውነቱን በአጭሩ እንደሚከተለው እናስቀምጣለን፡፡ አንድነት ፓርቲ ታህሣሥ 19 እና 20 ቀን 2006 ዓ.ም ያካሄደውን የጠቅላላ ጉባኤ ሰነድ ለምርጫ ቦርድ ካስገባ በኋላ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 20 ቀን 2006 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ በዘጠኝ ነጥቦች ላይ ማብራሪያ እንድንሰጥ ጠይቄን መልስ ሰጠን፤ በመቀጠልም ጥቅምት 2ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄ ከዘጠኝ ወደ ሦስት አውርዶ ላከልን ለዚህም አንድነት መልስ ሰጠ፡፡ ቀጥሎም ቦርዱ ህዳር 10 ቀን 2007 በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄውን ወደ አንድ አወረደው እንዲያውም በመጨረሻ ህዳር 19 ቀን 2007 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ። «ፓርቲው በሰጠው ምላሽ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ብዛት 320 እንደሆነ አሳውቋል። ይሁን እንዷ በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ አካቶ ያላቀረበ በመሆኑ ይህንኑ አሟልታችሁ እንድታቀርቡ በአክብሮት እናሳውቃለን» የሚል ነው። እኛም ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተን ይህንኑ ጥያቄ እንዲሟላ ከማድረጋችንም ባሻገር በሕገ-ደንባችን መሠረት በብሔራዊ ም/ቤት ተመርጠው የነበሩት የፓርቲውን ፕሬዚደንት ሹመት በጠቅላላው ጉባኤ አፀድቀናል። እንጂ አይነቱን በሕገ-ደንቡና በሥነ-ሥርዓት ለተከናወኑ ጉዳዮች ያልተገባና የተሳሳተ መግለጫ መስጠት በጣም አሳኝ ነው። በተለይም የሕዝብ ታዛቢዎች ታህሣሥ 12 ቀን 2007 ዓ.ም እንደሚመረጡ እየታወቀ ይህን ዓይነት መግለጫ መስጠት ሕዝቡ በጥንቃቄና በተደራጀ ምልኩ ትክክለኛነትና ሀቀኞች የሆኑ ታዛቢዎችን እንዳይመርጥ ለማሰናከል የታቀደ ይመስላል። በመሆኑም ዛሬም ሆነ ነገ አንድነት ፓርቲ ከሕዝብ ጋር ሆኖ ትግሉን አጠንክሮ ይቀጥላል አባላትም ሆነ ሕዝቡ ከፓርቲያችን ጎን ተሰልፎ ትግሉን እንዲያጧጡፈው ከአክብሮት ጋር እንጠይቃለን።
ድል የህዝብ ነው!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

torsdag 18. desember 2014

ንግድ ባንክ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርን ከስራ አገደ

የሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ እያስፔድ ተስፋዬ ከሚሰራበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአዳር ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ በደረሰበት እስር ምክንያት ከስራው ታገደ፡፡ እያስፔድ ተስፋዬ በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ጨለማና ቀዝቃዛ ክፍል ታስረው ከነበሩት አመራሮች መካከል አንዱ ሲሆን ከእስር ከተፈታ በኋላ ታስሮ ስለመቆየቱ ማስረጃ ቢወስድም ለ15 ቀን ከስራ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጓል፡፡

‹‹ታስሬ መቆየቴን የሚያሳይ ማስረጃ ወደምሰራበት ቅርንጫፍ ስወስድ ከእኛ አቅም በላይ ስለሆነ ወደ ዲስትሪክት ውሰድ ተባልኩ፡፡ ዲስትሪክት ስወስድ የንግድ ባንክ ዳይሬክተር የሰው ኃይል አስተዳደር ማመልከቻና ታስረህ የቆየህበትን ማስረጃ አስገባና እነሱ ወደ ስራ ገበታህ ተመለስ ካሉህ ነው የምትመለሰው፤ እነሱ ተመለስ እስኪሉህ ድረስ ግን ወደ ስራ ገበታ መመለስ አትችልም አሉኝ፡፡ ባሉኝ መሰረትም ለሰው ኃይል አስተዳደር ደብዳቤና ከፖሊስ ጣቢያ የተሰጠኝን ማስረጃ ወሰድኩ፡፡ ዳይሬክተሩ እስኪያየው ድረስ ተብሎ አንድ ቀን ቀጠሮ ተሰጠኝ›› የሚለው እያስፔድ በቀጠሮው መሰረት ሲሄድ ጉዳዩ ለቅሬታ ሰሚ ኮሜቴ እንደተላከ፣ ነገር ግን የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባሎች ስልጠና ላይ በመሆናቸው ለ15 ቀን ስራ መግባት እንደማይችልና ለታገደበት ቀናትም ደመወዝም እንደማይከፈለው እንደተገለጸለት ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድቷል፡፡

ቀደም ሲል የሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ አቶ ወሮታው ዋሴ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተባረሩ መሆናቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

በአዳር ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ምክትል ፀኃፊ ህይወታቸው አደጋ ላይ ነው

በአዳር ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ምክትል ፀኃፊ መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ ራሳቸውን ስተው ሆስፒታል እንደገቡና ሕይወታቸው አደጋ ውስጥ እንደሆነ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ሽዋንግዛው ገ/ስላሴ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በአዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን ለአምስት ቀናት ቀዝቃዛና ጨለማ ቤት ውስጥ ታስረው ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ የስኳር በሽታ መድሃኒታቸውን በመቀማታቸውና ህክምናም ባለማግኘታቸው ታመው እንደነበር ለማወቅ መገለጹ ይታወሳል፡፡

መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በድብደባውና በስኳር በሽታ ምክንያት በአሁኑ ወቅት ዘውዲቱ ሆስፒታል የሚገኙ ሲሆን ሆስፒታል ከገቡበት ቅዳሜ ታህሳስ 4/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሰው ማናገር አለመቻላቸውን የፓርቲው ፕሬዝዳንት አክለው ገልጸዋል፡፡


ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

torsdag 11. desember 2014

በሃገራችን ላለው ችግር የሴቶች ተደራጅቶ መታገል አስፈላጊ እና ወቅታዊ ምላሽ ነው፦

ዛሬ ዛሬ ከረጅም አመታት ጀምሮ በሃገራችን የተነሳው የሴቶች መብት ይከበር የሚለውን ይህዝብ ጥያቄ
ለመቃረን እስኪመስል ድረስ ከባለፉትም ጊዜያቶች በባሰ ሁኔታ የሴቶች መብት እየተጣሰ ይገኛል።
ከዛም አልፎ ተቆርቋሪ አካል የሌላቸው የሃገራችን ሴቶች ህይወታቸው አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ለዚህም በየጊዜው ወደ ተለያዩ አፍሪካና አረብ ሃገራት በተለይም በሱዳን በየመን የሚፈልሰው
የኢትዮጵያውያን ሴቶ ች ቁጥር መጨመር ማረጋገጫ ነው። በተለያዩ በሱዳን በየመንና በተለያዩ አረብ
ሃገራት ያሉ ሴቶች እህቶቻችን ተጠሪ እንደሌላቸው በመገመት የየሃገራቱ ዜጎች እና መንግስታት
እንደፈለጉ ሲያሰቃዩዋቸው እያየን ያለነው እውነታ ነው። ተጠሪ እንደሌላቸውም በቅርቡ በወያኔ ኤምባሲ
ፊለፊት ተደፍራ የተጣለችው እህታችን እና ወደዛው አካባቢ እየደረሰ ያለው ስቃይ እና የስርአቱ ምላሽ
ማረጋገጫ ናቸው። ሌላው መቼ ከእኛ ከ ኢትዮጵያውያን አዕምሮ የማይወጣው በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ
በእህቶቻችን የደረሰው ግፍ እና ብሄራዊ ውርደትን ተያይዞ መንግስታችሁ ነኝ ባዩ የሰጠው ምላሽ
የምትፈልገውን ለም መሬት ከኢትዮጵያ በመውሰድ በስርአቱ ተጠቃሚ የሆነችው ጎረቤት አገር ሱዳን
በኢትዮጵያውያን ሴቶች እየተፈጸመ ያለው በደል መቼም ቢሆን ከእኛ ሴቶች ብቻ ሳንሆን ኢትዮጵያዊ
ለሆነ ሁሉ የእግር እሳት እንደሆነ ነው። የእነዚህ ሃገራትህዝብ እና መንግስታት እንደፈለጉ መሆናቸው
የወያኔን ለቡድን እንጂ ለህዝብ ዴንታ ቢስነት መገንዘባቸው ይመስላል። ለነገሩ በውጭ ሃገራት አልን
እንጂ ኢትዮጵያውያን ሴቶች በ።ሃገራቸው የሚደርስባቸ መከራ እና እንግልት ከቀን ወደቀን እየተባባሰ
ነው።እንደውም የዚህ ስርአት ዋና ተጠቂ ሴቶች መሆናቸውን በመዲናችን አዲስ አበባ በገሃድ የሚታይ
ነው።አዲስ አበባ ዓለም ዓቀፍ ከተማ እንደመሆኗ እንግዶችን ሊስብ የሚችሉ በርካታ ሰራዎችን መስራት
እየተቻለ ለወገን ለሃገር እና ስለነገው የማያስበው ይህ ስርዓት ለዚሁተግባር ደላሎችን በማሰማራት እና
የተለያዩ ነገሮችንበመጠቀም ቆነጃጅት እህቶቻችንን ለተርካሻ ስራ እያሰማራ ይገኛል።ከዚህም ሌላ በዚሁ
ሃገር አጥፊ ስርአት ባመጣው ቅጥያጣ ሙስና መስፋፋት የአስተዳደር ብልሹነት እና ብቃት ማነስ የተነሳ
በተፈጠረው የኑሮ ውድነት ታዳጊ ሴቶች ሳይቀሩ ኑሮን ለማሸነፍ ስጋቸውን ሸጠው ለመኖር መገዳደቸው
በመዲናችን ጎዳና እየታየ ያለ ሃቅ ነው።ይህ ትውልድን ጎጂ ተግባርም በአሁኑ ወቅት ወደ ተለያዩ ሃይ
ስኩል እና ኤለመንተሪ ትምህርት ቤቶች አቅራቢያ እየተስፋፋ ይገኛል። በበርካታ የአዲስ አበባ ት/ቤቶች
አካባቢ የሺሻ የጫት እና የመጠጥ ቤቶች ንግድ ተጧጡፏል።የነዚህ ነገሮች በትምህርትቤቶች አካባቢ
መስፋፋት ደግሞ ታዳጊዎችን ወደ አላስፈላጊ መንገዶች መምራቱ የታወቀ ነው። ይህም ተጽእኖ በሴቶች
እህቶቻችን ላይ የሚያደርሰው ጉዳት መጠነ ሰፊ ነው። ለዚህም ጉዳይ ስርአቱ መደሰቱን ለወላጆች ጩከት
ዝም በማለት እና ስለጉዳዩ ሲነሳ ጆሮ ዳባልበስ በማለት አረጋግጦልናል። በቅርቡ በታዳጊዋ ሃና ኦላንጎ
ላይ የደረሰው ግፍ የተሞላበት ድርጊት የዚህ ማረጋገጫ ነው። እንደዚሁም ስርዓቱ ለሴቶች ምንም ትኩረት
እንዳልሰጠ በርእዩተ አለሙ፤ በማህሌት ፋንታሁንና ኤዶም ካሳዬ እንዲሁም በሌሎቹም ስርዓቱን
በመቃወማቸውና በብዕራቸው የስራአቱን እኩይ ሴራ ስላጋለጡ በእስር ቤት የሚደርስባቸው መከራ እና
እንግልት ማረጋገጫ ነው።
የሆነው ሆኖ ሃያሶስት ዓመት ያስቆጠረው የጥፋት ስርዓት አንድም ቀን ለሴቶች መብት ሲቆም አላየንም
አንድም ደረጃ የሴቶችን መብትሲያሻሽል አላየንም ያሻሽላል ብለንም አንጠብቅም።የነሰምሃር እና
መሳዮዎቹዋ እና የስርዓቱ ተጠቃሚዎች ቅምጥል ኑሮ እና እንክብካቤ የአብዛኛው የስርዓቱ ሰለባ እና
የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆነውን ሴቶች ኑሮና የመብት ደረጃ ሊወክል አይችልም። እንደውም ማስተዋል
ለቻለ ይህ ስርአት በቆየ ቁጥር አሁን ላይ በሃገራችን ሴቶች ላይ ያለው ጥቃት ምን ደረጃ ሊደርስ
እንደሚችል መገመት ይችላል።
ታዲያ የዚህ ስርአት ለጥፋት መነሳትን የተረዳን እና የጥፋቱ ሰለባ የሆንን ሴት ኢትዮጵያውያን ከያለንበት
ተሰባስበን ስለመፍትሄው ልንወያይበት የሚገባበት፤ እንዲሁም ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት የምንደራጅበት
ጊዜ አሁኑኑ መሆን አለበት። ለዚህም በመጀመሪያ አሁን በስልጣን ላይ ያለው ስርአት ፍጹም የህዝብ እና
የሃገር ጠላት መሆኑን ማወቅ እና ማረጋገጥ፤ መፍትሄውም ይህን አጥፊ ቡድን ከህዝባችን ጫንቃ ማውረድ
በሚለው ቁርጥ አቋም ላይ መስማማት ይኖርብናል። ጠላትችን ከሆነው አምባገነናዊ ስርአት ጋር
ለምናደርገው እልህ አስጨራሽ ትግል በድል እንወጣ ዘንድ የሴት የጀግኖቻችንን ትግል ታሪክ መመርመርና
ማወቅ ወሳኝ በመሆኑ ገድላቸውን በማውሳት ልንማማር ይገባልም እላለሁ። እንደነ እቴጌ ጣይቱ እና
ሌሎችንም ተጋድሎ በማስታወስ እኛም የነሱ አብራኮች መሆናችንን ባለመዘንጋት እንደነሱ ታሪክ መስራት
እንደምንችል በማመን ትግላችንን መጀመር ይኖርብናል። ስርአቱን ከማስወገድ ባሻገር በአገራችን
የተከሰቱት ያለፉት ታሪካዊ ስህተቶቻችንን እንዳይደገሙ ቆም ብለን እያሰብን ለወጠነው ዲሞክራሲያዊ
ስርአት እኛ ሴቶች ተደራጅቶ ለመታገል መነሳት አለብን። የኛ የትግል ተሳትፎ በአገራችን እየተቀጣጠለ
ባለው ህዝባዊ ትግል ላይ ሲደረብ የሚኖረው ሚና ቀላል አይደለም። ስለዚህ ስርዓቱ ከሃገራችን ተወግዶ
የህዝብ መብት ይከበር ዘንድ ህዝባዊ እና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ትመሰረት ዘንድ እኛ ሴቶች
ተደራጅተን በመነሳት የበኩላችንን የትግል አሻራ እናበረክት ዘንድ ወገናዊ ጥሪየን አቀርባለሁ።
ህዝብ ያሸንፋል!!!

onsdag 10. desember 2014

የህወሃት የጦር አበጋዞች – የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ፂዬን ዘማርያም)

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (Metals and Engineering Corporation (METEC)
በመከላከያ ሚኒስትር ስር የሚገኘው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ብኢኮ/ሜቴክ)፣ሲጀምር አስራሁለት የሚደርሱ የተለያዩ ከደርግ/ወታደራዊው መንግስት በተወረሱ ፋብሪካዎችን ሥራ የጀመረ ድርጅት ነው፡፡ ሜቴክ በ2010 እኤአ በአስር ቢሊዩን (10,000,000,000)ብር መነሻ ካፒታል የተመሠረተ ድርጅት ነው ይሉናል፡፡ በአሁኑ ግዜ በህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ዘመን ከስባ አምስት ፋብሪካዎች በላይ ያሰባሰበ ድርጅት ለመሆን ችሎል፡፡ ሜቴክ ኮርፖሬሽን ከ13,000 ሠራተኞች ሲኖሩት ከነዚህ ውስጥ 1,000 ዎቹ ማሃንዲሶች ናቸው፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሃገሪቱን የኢኮኖሚ ትስስር መሪ ዶክተር ደብረፂዋን ገብረሚካኤል ሜቴክ በሃገር ውስጥና ከባህር ማዶ ሃገራት የቢዝነስ አጋሮቹ ጋር በመሆን ወደሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርትና ሸቀጦችን በመተካት የውጭ ምንዛሪ ለማዳን ሜቴክ ይንቀሳቀሳል ቢሉም ሜቴክ የሰራው ምርትና ያዳነው የውጭ ምንዛሪ ደፍረው አልገለፁም፡፡ ሜቴክ መንግስታዊ ሞኖፖሊ እንደሆነ የግሉን ዘርፍ ስራ እየነጠቀ እንደሆነ ዶክተሩ የሚመሩት ቴሌኮም ከዓለማችን ካሉ ሃገራት የመጨረሻ ተርታ ውስጥ መሆኑን መረዳት የተሳናቸው ኢንተርኔት አጠቃቀም ባለመቻላቸው ነው ተብለው ይታማሉ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ውሳኔዎችን አስተላለፈ

• ‹‹አገዛዙ የወሰደውና ወደፊት የሚወስደው ከእስካሁኑ የባሰ አረመኔነት እርምጃ ይበልጡን ያጠናክረናል››
የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ትናንት ህዳር 30/2007 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ትግሉን ያጠናክራሉ ያላቸውን ውሳኔዎችን አስተላለፈ፡፡ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ያስተላለፋቸው ውሳኔዎች ‹‹ህወሓት/ኢህአዴግ በፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እና እስር ምክንያት ክፍተት ሳይፈጠር የፓርቲው እንቅስቃሴ እንዲቀጥልና ትግሉም እንዲጠናከር የሚያስችሉ ናቸው›› ሲሉ የብሄራዊ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰይድ ኢብራሊም ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ብሄራዊ ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ ህወሓት/ኢህአዴግ በአመራሩ፣ አባላቱና ደጋፊዎቹ ላይ የፈጸመው ጭካኔ ለሰላማዊ ታጋዮች ባለው ጥልቅ ጥላቻና ጭካኔ በተሞላበት እርምጃው ከትግሉ ያፈገፍጋሉ ከሚል ስሌት እንደሆነ በመግለጽ ‹‹አገዛዙ የወሰደውና ወደፊትም ሊወስደው የሚችለው ከእስካሁኑ የባሰም አረመኔነት የተሞላበት እርምጃ ይበልጡን ያጠናክረናል እንጅ ከትግላችን ቅንጣት ያህል ወደኋላ እንደማናፈገፍግ›› ብሏል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በአንድ በኩል ‹‹ምንም ችግር ሳይፈጥሩ በቁጥጥር አዋልናቸው›› ያላቸውን ሰላማዊ ታጋዮች በሌላ በኩል ፍርድ ቤት አቅርቦ ‹‹መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውደመዋል›› ሲል መክሰሱም በገዥው ፓርቲ የሚዘወሩ ተቋማት በጉዳዪ ላይ አንድ አይነት አቋም እንደሌላቸውና ይህም የተጀመረው ሰላማዊ ትግል ስርዓቱን መያዣ መጨበጫ እንዳሳጣው ያሳያል ብሏል፡፡
ከህወሓት/ኢህአዴግ ከዚህ የባሰ ጭካኔን እንጠብቃለን ያለው ምክር ቤቱ ‹‹በምናደርገው ትግል ሁሉ የሚጠበቅብንን መስዋእትነት ለመክፈልና ሀገራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ መሆናችን እየገለጽን መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጀንለትና የምናከብረው ህዝብ ከጎናችን እንዲቆም›› ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ምክር ቤቱ እሁድ ታህሳስ 5/2007 ዓ.ም መደበኛ ስብሰባ የጠራ ሲሆን የተላለፉት ውሳኔዎች በምን መልኩ ተግባራዊ እንደሚሆኑ ተወያይቶ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
source Negere Ethiopia