fredag 18. april 2014

ወቅታዊ ሪፖርት በኖርዎይ:

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ የሚገኙ ኢትዮጵያን ስደቶኞች የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው የሚኖሩበት ሃገር እንደሚሰለሉ እና የወያኔ ሰላዮች በኖርዎያ እንደሚገኙ የኖርዎይ ደህንነት ፖሊስ ለሃገሩ ትልቅ መረጃ መስጠታቸውን በተመሳሳይ ሂውማን ራይትስ ዎች በቅርቡ ያወጣውን መረጃ መሰረት በማድረግ የኖርዎይ መንግስታት ለወያኔ ሰላዮች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆም እና አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ለመጠየቅ እና ኖርዎይ በኢትዮጵያውያን ላይ ያላትን አሳይለም ፖሊሲ እንድታስተካክል በሚል የጠራውን ሰልፍ እጅግ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ይህ ሰልፍ የኢትዮጵያን በኖርዎይ ምን ይህል የሃገራቸው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው እና እየታገሉ እንደሆነ የሚያሳይ ሰልፍ ነበረ። ከኖርዎይ ጂኦግራፊያዊ ይዘት አንጻር ለመሰባሰብ አስቸጋሪ ቢሆንም ኢትዮጵያውያን ግን ይህንን ችግር ከምንም ሳይቆጥሩት ድምጻቸውን እንዳሰሙ ይገኛሉ በርቱ የሚያሰኝ ነው። በሌላውም ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደ ኖርዎይ አንድ ሆነው ድምጹ የታፈነውን ህዝባችንን ድምጽ ሊሆኑለት ይገባል።











በኖርዎይ ዋና ከተማ ኦስሎ ከተለያዩ ቦታ በተሰባሰቡ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በየጊዜው
የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ ማስተናገዱን ተያይዘዋለች። በኖርዎይ የሚገኙ ጠንካራ
ተቃዋሚ ድርጅቶች በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት, የኢትዮጵያ
ስደተኞች ማህበር ትልቁን ሚና ይጫወታሉ። እነዚህ የተለያዩ ድርጅቶች ለሚያዘጋጁት
ሰልፎች መሳካት ደግሞ በኖርዎይ ነዋሪ የሆኑ እና በተለያዩ ካንፕ ውስጥ የሚገኙ ሃገር ወዳድ
ኢትዮጵያውያን ተጠቃሽ ናቸው። ዓርብ አፕሪል 11 2014 ያየንው ይህንንው ነው። በዚህ
ዕለት የኢትዮጵያውያ ሰደተኞች ማህበር የጠራውን ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር። ሠልፉ
የሚጀምረው ከቀኑ 12 ሰአት ይሁን እንጂ በሀገሩ ወቅታዊ ሁኔታ የሚንገበገበው ሀገር ወዳድ
ኢትዮጲያዊ ከተባለው ሰአት በፊት ጥሪ በተደረገበት ቦታ ተሰባስቦ የፕሮግራሙን መጀመር
ሲጠባበቅ ነበር። የተባለው ሠአት ሲጀምር የዝግጅቱ አስተባባሪዎች የእንኳን ደህና
መጣችሁና የዝግጅቱን አላማ በማስተዋወቅ ዝግጅቱ ጀምሯል። ልክ ንግግሩ እንዳለቀ
በፕሮግራሙ መሰረት ያለውን ችግር ወደ ሚያስረዳበት ፖርላማ ጉዞውን አድርጎዋል።
ህዝቡም ፖርላማ እስከሚደርስ ድረስ የተለያዩ መፈክሮችን እያሰማ ነበር። በሰልፉ ላይ
የተሳተፈው ህዝብም መፈክሩን የሚያሰማው እጅግ ከልቡ ተቆጥቶና በከፍተኛ ጩኸት ነበር።
በዚህ ወቅትም በጎዳና ላይ የነበሩ ኖርዊጅያኖች በመገረም መንገዳቸውን ትተው ቆመው
ሲያስተውሉ ነበር። አንዳንዶችም ካሜራቸውንና ሞባይላቸውን ወደ ሰልፈኛው ቀስረው
ለረጅም ሰአት ሲቀርጹ ነበር። በዚህ ሁኔታ ወደ ፓርላማው ከተደረሰ በኌላ የተለያዩ
ግለሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ስለ ወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ እና ስለሰልፉ አላማ
ንግግሮች አድርገዋል። ሠልፉን በተመለከተም መልዕክታቸውን ከፓርላማ ለተላኩት ግለሰብ
ሠጥተዋል።

            አፕሪል 12/2014 በኖርዌ ኦስሎ ከተማ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ
የድጋፍ ድርጅት አዘጋጅነት የአትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እንደዚሁም የዲያስፖራው
የትግል ተሳትፎን የዳሰሰ ታላቅ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚህ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ በርካታ
አትዮጵያውያን ተገኝተዋል።













ለ6 ሠዓታት ያህል የተካሄደው ይህ ስብሰባ የጀመረው በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆኑት አቶ አቢ አማረ ጋባዥነት በሀገራችን ባለው በዘረኛው አረመኒያዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ እስር ቤቶች በፓለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ያለጥፍታቸው ያሚሰቃዩትን ውድ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችንን በማሰብ በዚሁ ዘረኛ ቡድን ሰለባ ለሆኑ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማድረግ ነበር። በመቀጠል አቶ ዩሀንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር አድርገዋል።
በዚህ ስብሰባ ላይ የእለቱ ተጋባዥ እንግዳ የሆኑት የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ብዙነህ ጽጌ የተገኙ ሲሆን በሃገራችን ስላለው ጠቅላላ የፖለቲካ ሁኔታ እና የግንቦት 7ን አስተዋጽኦ ከህዝቡ የሚጠበቀውንም አጠቃሎ እጅግ ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል። በዝግጅቱ ላይ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት አባሎች ‘’ላንቺ ነው ሃገሬ’’ የሚለውን መዝሙር አቅርበዋል።














ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!!!

lørdag 12. april 2014

ሒላሪ ክሊንተን ጫማ ተወረወረባቸው ( ቪዲዬ )



በመጪው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነው ይቀርባሉ እየተባሉ የሚጠበቁት ሒላሪ ክሊንተን ንግግር በሚያደርጉበት ጊዜ ጫማ ተወረወረባቸው፡፡ ጉዳት ባይደርስባቸውም ዜናው ግን የበርካታ ሚዲያዎችን ቀልብ ስቧል፡፡
አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው የቀድሞው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሒላሪ ክሊንተን በላስ ቬጋስ በተጠራ የመልሶ መጠቀም ኢንዱስትሪዎች (Scrap Recycling Industries) ስብሰባ ላይ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ባላሰቡት እና ባልጠበቁት ሁኔታ ከአዳራሹ ጫማ ተወርውሮባቸዋል፡፡
ጫማው ሳይመታቸው ቢቀርም ወርዋሪዋ ግለሰብ አስተካክላ ብትወረውር ግን ክፉኛ ጉዳት ልታደርስባቸው ትችል እንደነበር የቪዲዮው ምስል ያመለክታል፡፡ ምክንያቱም በወቅቱ አዳራሹ ጨለምለም ያለ በመሆኑ ክሊንተን ጫማው ከተወረወረ በኋላ ነው ያስተዋሉትና ደበቅ ለማለት የሞከሩት፡፡
ሒላሪ ክሊንተን በጉዳዩ ላይ ቀልድ በማከል አስተያየት የሰጡበት ቢሆንም የስብሰባው ኃላፊዎች ግን ታላቅ ይቅርታ ጠይቀዋቸዋል፡፡ ጫማ ወርዋሪዋ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር የዋለች ከመሆኗ በላይ ማንነቷ ገና አልተገለጸም፡፡
የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን ሚስት ሒላሪ ከፍተኛውን የፖለቲካ ሥልጣን ለመቆናጠጥ በዝግጅት ላይ እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በነበሩበት አራት ዓመታት ያከናወኗቸው በርካታ ሥራዎች እንዳሉ ደጋፊዎቻቸው ቢጠቀሱም የጋዳፊ ግድያ ከዚያም ጋር ተያይዞ የተከሰተው የቤንጋዚው ቀውስ እና የአሜሪካው አምባሳደር መገደል፣ በግብጽ የተካሄደው ለውጥና ከዚያም በአሜሪካና ምዕራባውያን ግፊት ለውጡ መቀልበሱ፣ በአፍጋኒስታንና ፓኪስታን ላይ የወሰዱት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ በአፍሪካ እንደነ መለስ ካሉ አምባገነኖች ጋር በመሞዳሞድ ግብረሰዶማዊነት እንዲስፋፋ አሜሪካ የተከተለችው ፖሊሲ፣ ወዘተ በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ሒላሪ ኪሊንተን በቅርቡ በውጭ ጉዳይ ሚ/ርነት ዘመናቸው ስላከናወኑት የሚያወሳ “የሚኒስትር ማስታወሻ” በገበያ ላይ ያውላሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
የዛሬ ስድስት ዓመት አካባቢ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ በኢራቅ ከጠ/ሚ/ር ኑሪ አልማላቂ ጋር ንግግር ሲያደርጉ አገሩ በአሜሪካ ወራሪነት መፍረሷ ያናደደው ኢራቃዊ ጋዜጠኛ የጫማ ሚሳኤል ወርውሮባቸው እንደነበር አይዘነጋም፡፡
http://www.goolgule.com/shoe-thrown-at-hillary-clinton-at-vegas-speech/

mandag 7. april 2014

ህወሀት ኢሕአዴግን ለማገልገል ህዝባቸውን የሚጨፈጭፉ ሎሌዎች (በሁኔ አቢሲኒያዊ)


(ክፍል ሁለት)
በክፍል አንድ የወያኔውን ሎሌ ባጫ ደበሌን ብልሹ ስራዎች አይተናል ዛሬ 180 ዲግሪ ዞሮ የወያኔ አሽከር ስለሆነው ሬድዋን ሁሴን አንዳንድ ነገሮች እንላለን፡፡
መልካም ንባብ
አቶ ሬድዋን የ1987 ዓ.ም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የባዮሎጂ ምሩቅ ናቸው። ከምረቃ በኋላ ለማስተማር ጂንካ የተወሰነ ጊዜ አሳልፈዋል። ደቡብ ኢትዮጵያ ብዙም አልቆዩም። አዲስ አባባ መጥተው አወሊያ ትምህርት ቤት መምህር ኾኑ። የአወሊያ ትምህርት ቤት ቆይታቸው አስደሳች የኾነም፤ ያልኾነም ነበር። ከትምህርት ቤቱ አስተዳደር ጋራ በተደጋጋሚ ይጋጩ እንደነበር ይነገራል። በ1980ዎቹ መጨረሻ እና በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ የስልጤን የማንንት ጥያቄ በዋናነት በማቀንቀን ይታወቃሉ። “ስልጤ በደቡብ ክልል ውስጥ ውክልና ይገባዋል
ከሚለው አልፎ በዞን ደረጃ እንዲዋቀር ተሟግተዋል።” በወቅቱ በርካታ የስልጤ ተወላጆችን በቅርብ ማግኘት በመቻላቸው በጉዳዩ እንዲገፉበት ዕድል ሰጥቷቸዋል። በዚያውም የስልጤ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ስሕዴፓ)ሲያቋቁም ከመሪ ተዋንያኑ አንዱ ሆነው ብቅ አሉ፡፡
ኢሕአዴግም እንደለመደው በአሁኑ የመከላከያ ሚኒስቴር እና የቀድሞ የአለማያ ዩኒቨርስቲ የደን ልማት(ፎረስትሪ) ጥናት ተማሪ በነበሩት አቶ ሲራጅ ፈጌሳ የሚመራውን “የስልጤ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት” (ስሕዴድ) አቋቋመ። ሁለቱ የስልጤ ሕዝብ ድርጅቶች እርስ በርስ ይፎካከሩ ሲልም በግልጽ ይተቻቹ ነበር። ፀባቸው ሌላ አይደለም። እውነተኛ የስልጤ ሕዝብ ተወካይ ማን ነው?የሚለው ነው። ሬድዋን የእነ አቶ ሲራጅን ስሕዴድ፣ “አሻንጉሊት” እና “የኢሕአዴግ ተላላኪ” በማለት እስከ እስከ መወጀል ይደርሱ እንደነበር ይነገራል።
በ1992 ዓ.ም “የስልጤ ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እና ከጉራጌ ሕዝብ የተለየ ማንነት ያለው መኾኑ በሕዝብ ውሳኔ ሲረጋገጥ የአቶ ሬድዋንም ሚና እና የፖለቲካ አቅጣጫ ተቀየረ።” ይላሉ ለአዲስ ነገር ሐሳባቸውን ያካፈሉት ውስጥ አዋቂ። በ1992 በተደረገው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ የሬድዋን ፓርቲ ከደቡብ ክልል ስልጤ ዞን ተወዳድሮ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገቡ። ሬድዋን በፓርላማ በቆዩባት አጭር ወቅት በኢሕአዴግ ምን ያህል እንደ ተዋጡ ተገነዘቡ። ለፖለቲካ ግባቸው ስሕዴፓ ሳያንስባቸው አልቀረም።
ፓርላማ ከገቡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሬድዋን እና ጓዶቻቸው ስሕዴፓን አፍርሰው ድሮ ሲተቹት የነበረውን የአቶ ሲራጅን ስሕዴድ ተቀላቀሉ። የፓርላማ ውክልናቸውን ጥለው “የስልጤ ዞን የሕዝብ ጉዳዮች አደረጃጀት” ሐላፊ በመኾን እስከ 1997 ዓ.ም ድረስ ቆዩ። በ1997 ዓ.ም ከስልጤ ዞን ለደቡብ ክልል ምክር ቤት በመወዳደር የደቡብ ክልል ምክር ቤትን ተቀላቀሉ። ከዚያ በኋዋላ ነው የደቡብ ክልል ምክር ቤት የትምህርት ቢሮ ሐላፊ ብሎም የደኢሕዴን የሥራ አስፈጻሚነትን የተቀላቀሉት።
የስልጤ ዞን በምርጫ 97 ልክ እንደ ደሴት ነበረች። በዙሪያው የነበሩት አጎራባች ክልሎች በአብዛኛው የኢሕአዴግን ተቃዋሚዎች የመረጡ ሲኾን ስልጤ ግን ስህዴድን/ደኢሕዴን/ኢሕአዴግን መርጣለች። በ97 ዓ.ም የነበረው የተቃዋሚዎች ማዕበል ጉዟቸውን አፋጥኖላቸዋል። በአምስት ዓመት ውስጥ ከወራቤ ከተማ ተነስተው የኢሕአዴግ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ “ወንጌል” ዋና አጥማቂ ኾነው ወጡ፤ በምድረ በዳ የሚጮሁ።
ኢሕአዴግ “ዱላ መቀባበል” በሚለው ጨዋታ “የፊት መሥመር ተሰላፊ የነበሩት ወደ ኋላ ኾነው፣ የድርጅት ሥራ የሚሠሩት ወደ ፊት የሚመጡበት ነው” በሚለው መሠረት “ትጉህ ባርያ” የነበሩት አቶ ሬድዋን የአቶ በረከት ስምዖን ቦታ ያዙ ተብሎ ። የሬድዋንም የተስፋ ምድር ይህች ነበረች። የአቶ በረከትን ቦታ ማግኘት
አቶ ሬድዋንን ኢሕአዴግ ግንባር ቀደም የምርጫ ተከራካሪ አድርጎ ለማምጣት በፓርቲው ውስጥ በዚሁ ታሪካቸው የተነሳ የሐሳብ ልዩነት እንደነበር ይነገራል። “ድሮ ይቃወመን በነበረ ሰው መወከል!” በሚል። ዋናው ነገር ሬድዋን ሥራቸውን አይዘነጉም። “የተለያዩ ማኅበራትን ታደራጃለህ”፤ “ከጀርባ ትቆጣጠራለህ”፤ የሚለው የፖለቲካ ቅኝት እየተሰጣቸው ለሚፈልገው ዓላማ ይሰናዳሉ። አቶ ሬድዋንም ይህችን አሠራር ከአዲስ አባባ የክፍለ ከተማ ስበሰባዎች፣ በፍቼ እና በአላጌ ተግብረዋታል። የአዲሱ በረከት ጠንካራ ጎኑም ይህ ነው።
እነ አቶ ሕላዌ መሠረቱን የጣሉለትን ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ የሚወስድ ግንባር ቀደም ካድሬ ይፈለግ ነበር። ኢሕአዴግ ዐይኑን ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ጣለ። ደቡብ ኢትዮጵያ በፖለቲካ እና ሕዝብ አደረጃጀት “የተካኑ” የሚባሉ ሰዎችን ማፍራት ይዟል። አቶ ኀይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ካሊድ አሕመድ፣ ሬድዋን ሁሴን፣ መኩሪያ ኀይሌ ከሌሎቹ አጋር የኢሕአዴግ ፓርቲዎች በላቀ ጎላ ብለው መታየት ጀምረዋል።
በወቅቱ የደቡብ ክልል የትምህርት ቢሮ ሐላፊ፣ የደኢሕዴን ኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ ሬድዋን ሑሴን ደግሞ በተናጋሪነታቸው ይታወቃሉ። በዚያ ላይ የሕዝብ አደረጃጀት ልምድ አላቸው። የሁሉም ዐይን ሰውየው ላይ አረፈ። ሬድዋንም ወደ አዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ሐላፊነት ተመደቡ፡፡
ሥራው ቀላል እና ግልጽ ነው። “ፓርቲውን በሕዝብ ውስጥ ማሥረጽ።” “ከፍተኛ ቁጥር ያለው አባል መመልመል፤ የተመለመሉትንም ከእምነታቸው እንዳይናወጹ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን ማስረጽ – ሁለተኛ ተፈጥሯቸው እስኪመስል። ” በከተማው አስተዳደር ውስጥ የፓርቲ ሥራ ከመንግሥት ሥራ ጋራ የጨው እና የውኃ ያህል እስኪወሃዱ ድረስ ሬድዋን እረፍት የላቸውም። የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራጅተው የፓርቲውን ጥቅም በዘላቂነት እንዲያስከብሩ ይታትራሉ። ሬድዋን በሚመሩት የአዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ሥር የሚገኙ አራት ወሳኝ የመመልመያ እና መከታተያ መዋቅሮችን ይመራሉ። የአባላት ሥልጠና፣ አነስተኛ እና ጥቃቅን እና ትምህርት፣ ግብር መልስ እና ሱፐርቪዥን እና የሕዝብ አደረጃጀት ናቸው።
ሁኔ አቢሲኒያዊ
ኦክስፎርድ ዩ.ኬ

የጠበቆች ማህበር በአርቲስት ግሩም ኤርሚያስ ላይ የወንጀል ክስ መመስረታቸው ተሰማ


በአዲስ አበባ ታትሞ የሚወጣው ማራኪ መጽሔት እንደዘገበው በቅርቡ በሰይፉ ፋንታሁን የኢቢኤስ ሾው ላይ ቀርቦ በአዲስ ፊልሙ ላይ አደንዛዥ ዕፅ ተጠቅሞ መስራቱን ለማህበረሰቡ ያሳየው አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ የጠበቆች ህብረት በጋራ የወንጀል ክስ አቅርበውበታል።
ጠበቃ ማቲያስ ግርማ ለማራኪ መፅሄት እንዳስረዱት በክሱ ላይ ሰይፉ ፋንታሁንና አለማየሁ ታደሰ ደጋፊ ሀሳብ በመስጠታቸው ክስ ይመሰረትባቸዋል ብለዋል። አርቲስቱ ምንም እንኳ ለፊልም ግብዓት “መስለው ሳይሆን ሆነው” ለመስራት ያደረጉት ተግባር ቢሆንም ህብረተሰቡን ከወንጀል ለመጠበቅ ሲባል ክስ እንደተመሰረተባቸው የጠበቆች ተወካዩ አስረድተዋል።

“ይህንን የበለጠ ማጣራት የነበረባቸው ፖሊስና አቃቤ ህግ ቢሆኑም ፣ በግልፅ በሀገሪቱ የአየር ክልል የተላለፈውን መረጃ ዝም ማለታቸው እንዳሳዘናቸውም ገልፀዋል። በሀገሪቱ የወንጀል ህግ ስርዓት በተለይ ግሩም በክሱ ጥፋተኛ ከተባለ እስከ ሰባት አመት እንዲሁም የ50ሺ ብር ቅጣት ይጠብቀዋል።

በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ 1996/97 አንቀፅ 525 ንዑስ አንቀፅ/ሀ መሰረት እስከ ” አደንዛዥ ዕፅን እራሱ ወይም ሌላ ሰው ሊጠቀምበት በማሰብ የገዛ፣የተጠቀመ፣ እንዲጠቀም ያደረገ፣,,,” ከ7 ዓመት እስከ 50ሺ ብር ቅጣት ይጠብቀዋል። እነ ሰይፉ ደግሞ “ወንጀልን ባለማወቅ” ክስ ተመስርቶባቸዋል።
መጽሔቱ ዘገባውን ሲያጠናቅቅ ለግሩም በቅርብ መጥሪያ ይደርሰዋል ተብሎ ይጠበቃል ብሏል።
Ze-Habesha