የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ የሚገኙ ኢትዮጵያን ስደቶኞች የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው የሚኖሩበት ሃገር እንደሚሰለሉ እና የወያኔ ሰላዮች በኖርዎያ እንደሚገኙ የኖርዎይ ደህንነት ፖሊስ ለሃገሩ ትልቅ መረጃ መስጠታቸውን በተመሳሳይ ሂውማን ራይትስ ዎች በቅርቡ ያወጣውን መረጃ መሰረት በማድረግ የኖርዎይ መንግስታት ለወያኔ ሰላዮች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆም እና አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ለመጠየቅ እና ኖርዎይ በኢትዮጵያውያን ላይ ያላትን አሳይለም ፖሊሲ እንድታስተካክል በሚል የጠራውን ሰልፍ እጅግ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ይህ ሰልፍ የኢትዮጵያን በኖርዎይ ምን ይህል የሃገራቸው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው እና እየታገሉ እንደሆነ የሚያሳይ ሰልፍ ነበረ። ከኖርዎይ ጂኦግራፊያዊ ይዘት አንጻር ለመሰባሰብ አስቸጋሪ ቢሆንም ኢትዮጵያውያን ግን ይህንን ችግር ከምንም ሳይቆጥሩት ድምጻቸውን እንዳሰሙ ይገኛሉ በርቱ የሚያሰኝ ነው። በሌላውም ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደ ኖርዎይ አንድ ሆነው ድምጹ የታፈነውን ህዝባችንን ድምጽ ሊሆኑለት ይገባል።
በኖርዎይ ዋና ከተማ ኦስሎ ከተለያዩ ቦታ በተሰባሰቡ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በየጊዜው
የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ ማስተናገዱን ተያይዘዋለች። በኖርዎይ የሚገኙ ጠንካራ
ተቃዋሚ ድርጅቶች በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት, የኢትዮጵያ
ስደተኞች ማህበር ትልቁን ሚና ይጫወታሉ። እነዚህ የተለያዩ ድርጅቶች ለሚያዘጋጁት
ሰልፎች መሳካት ደግሞ በኖርዎይ ነዋሪ የሆኑ እና በተለያዩ ካንፕ ውስጥ የሚገኙ ሃገር ወዳድ
ኢትዮጵያውያን ተጠቃሽ ናቸው። ዓርብ አፕሪል 11 2014 ያየንው ይህንንው ነው። በዚህ
ዕለት የኢትዮጵያውያ ሰደተኞች ማህበር የጠራውን ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር። ሠልፉ
የሚጀምረው ከቀኑ 12 ሰአት ይሁን እንጂ በሀገሩ ወቅታዊ ሁኔታ የሚንገበገበው ሀገር ወዳድ
ኢትዮጲያዊ ከተባለው ሰአት በፊት ጥሪ በተደረገበት ቦታ ተሰባስቦ የፕሮግራሙን መጀመር
ሲጠባበቅ ነበር። የተባለው ሠአት ሲጀምር የዝግጅቱ አስተባባሪዎች የእንኳን ደህና
መጣችሁና የዝግጅቱን አላማ በማስተዋወቅ ዝግጅቱ ጀምሯል። ልክ ንግግሩ እንዳለቀ
በፕሮግራሙ መሰረት ያለውን ችግር ወደ ሚያስረዳበት ፖርላማ ጉዞውን አድርጎዋል።
ህዝቡም ፖርላማ እስከሚደርስ ድረስ የተለያዩ መፈክሮችን እያሰማ ነበር። በሰልፉ ላይ
የተሳተፈው ህዝብም መፈክሩን የሚያሰማው እጅግ ከልቡ ተቆጥቶና በከፍተኛ ጩኸት ነበር።
በዚህ ወቅትም በጎዳና ላይ የነበሩ ኖርዊጅያኖች በመገረም መንገዳቸውን ትተው ቆመው
ሲያስተውሉ ነበር። አንዳንዶችም ካሜራቸውንና ሞባይላቸውን ወደ ሰልፈኛው ቀስረው
ለረጅም ሰአት ሲቀርጹ ነበር። በዚህ ሁኔታ ወደ ፓርላማው ከተደረሰ በኌላ የተለያዩ
ግለሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ስለ ወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ እና ስለሰልፉ አላማ
ንግግሮች አድርገዋል። ሠልፉን በተመለከተም መልዕክታቸውን ከፓርላማ ለተላኩት ግለሰብ
ሠጥተዋል።
አፕሪል 12/2014 በኖርዌ ኦስሎ ከተማ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ
የድጋፍ ድርጅት አዘጋጅነት የአትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እንደዚሁም የዲያስፖራው
የትግል ተሳትፎን የዳሰሰ ታላቅ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚህ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ በርካታ
አትዮጵያውያን ተገኝተዋል።
በዚህ ስብሰባ ላይ የእለቱ ተጋባዥ እንግዳ የሆኑት የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ብዙነህ ጽጌ የተገኙ ሲሆን በሃገራችን ስላለው ጠቅላላ የፖለቲካ ሁኔታ እና የግንቦት 7ን አስተዋጽኦ ከህዝቡ የሚጠበቀውንም አጠቃሎ እጅግ ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል። በዝግጅቱ ላይ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት አባሎች ‘’ላንቺ ነው ሃገሬ’’ የሚለውን መዝሙር አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!!!
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar