(ክፍል ሁለት)

በክፍል አንድ የወያኔውን ሎሌ ባጫ ደበሌን ብልሹ ስራዎች አይተናል ዛሬ 180 ዲግሪ ዞሮ የወያኔ አሽከር ስለሆነው ሬድዋን ሁሴን አንዳንድ ነገሮች እንላለን፡፡
መልካም ንባብ
አቶ ሬድዋን የ1987 ዓ.ም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የባዮሎጂ ምሩቅ ናቸው። ከምረቃ በኋላ ለማስተማር ጂንካ የተወሰነ ጊዜ አሳልፈዋል። ደቡብ ኢትዮጵያ ብዙም አልቆዩም። አዲስ አባባ መጥተው አወሊያ ትምህርት ቤት መምህር ኾኑ። የአወሊያ ትምህርት ቤት ቆይታቸው አስደሳች የኾነም፤ ያልኾነም ነበር። ከትምህርት ቤቱ አስተዳደር ጋራ በተደጋጋሚ ይጋጩ እንደነበር ይነገራል። በ1980ዎቹ መጨረሻ እና በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ የስልጤን የማንንት ጥያቄ በዋናነት በማቀንቀን ይታወቃሉ። “ስልጤ በደቡብ ክልል ውስጥ ውክልና ይገባዋል
ከሚለው አልፎ በዞን ደረጃ እንዲዋቀር ተሟግተዋል።” በወቅቱ በርካታ የስልጤ ተወላጆችን በቅርብ ማግኘት በመቻላቸው በጉዳዩ እንዲገፉበት ዕድል ሰጥቷቸዋል። በዚያውም የስልጤ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ስሕዴፓ)ሲያቋቁም ከመሪ ተዋንያኑ አንዱ ሆነው ብቅ አሉ፡፡
ኢሕአዴግም እንደለመደው በአሁኑ የመከላከያ ሚኒስቴር እና የቀድሞ የአለማያ ዩኒቨርስቲ የደን ልማት(ፎረስትሪ) ጥናት ተማሪ በነበሩት አቶ ሲራጅ ፈጌሳ የሚመራውን “የስልጤ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት” (ስሕዴድ) አቋቋመ። ሁለቱ የስልጤ ሕዝብ ድርጅቶች እርስ በርስ ይፎካከሩ ሲልም በግልጽ ይተቻቹ ነበር። ፀባቸው ሌላ አይደለም። እውነተኛ የስልጤ ሕዝብ ተወካይ ማን ነው?የሚለው ነው። ሬድዋን የእነ አቶ ሲራጅን ስሕዴድ፣ “አሻንጉሊት” እና “የኢሕአዴግ ተላላኪ” በማለት እስከ እስከ መወጀል ይደርሱ እንደነበር ይነገራል።
በ1992 ዓ.ም “የስልጤ ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እና ከጉራጌ ሕዝብ የተለየ ማንነት ያለው መኾኑ በሕዝብ ውሳኔ ሲረጋገጥ የአቶ ሬድዋንም ሚና እና የፖለቲካ አቅጣጫ ተቀየረ።” ይላሉ ለአዲስ ነገር ሐሳባቸውን ያካፈሉት ውስጥ አዋቂ። በ1992 በተደረገው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ የሬድዋን ፓርቲ ከደቡብ ክልል ስልጤ ዞን ተወዳድሮ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገቡ። ሬድዋን በፓርላማ በቆዩባት አጭር ወቅት በኢሕአዴግ ምን ያህል እንደ ተዋጡ ተገነዘቡ። ለፖለቲካ ግባቸው ስሕዴፓ ሳያንስባቸው አልቀረም።
ፓርላማ ከገቡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሬድዋን እና ጓዶቻቸው ስሕዴፓን አፍርሰው ድሮ ሲተቹት የነበረውን የአቶ ሲራጅን ስሕዴድ ተቀላቀሉ። የፓርላማ ውክልናቸውን ጥለው “የስልጤ ዞን የሕዝብ ጉዳዮች አደረጃጀት” ሐላፊ በመኾን እስከ 1997 ዓ.ም ድረስ ቆዩ። በ1997 ዓ.ም ከስልጤ ዞን ለደቡብ ክልል ምክር ቤት በመወዳደር የደቡብ ክልል ምክር ቤትን ተቀላቀሉ። ከዚያ በኋዋላ ነው የደቡብ ክልል ምክር ቤት የትምህርት ቢሮ ሐላፊ ብሎም የደኢሕዴን የሥራ አስፈጻሚነትን የተቀላቀሉት።
የስልጤ ዞን በምርጫ 97 ልክ እንደ ደሴት ነበረች። በዙሪያው የነበሩት አጎራባች ክልሎች በአብዛኛው የኢሕአዴግን ተቃዋሚዎች የመረጡ ሲኾን ስልጤ ግን ስህዴድን/ደኢሕዴን/ኢሕአዴግን መርጣለች። በ97 ዓ.ም የነበረው የተቃዋሚዎች ማዕበል ጉዟቸውን አፋጥኖላቸዋል። በአምስት ዓመት ውስጥ ከወራቤ ከተማ ተነስተው የኢሕአዴግ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ “ወንጌል” ዋና አጥማቂ ኾነው ወጡ፤ በምድረ በዳ የሚጮሁ።
ኢሕአዴግ “ዱላ መቀባበል” በሚለው ጨዋታ “የፊት መሥመር ተሰላፊ የነበሩት ወደ ኋላ ኾነው፣ የድርጅት ሥራ የሚሠሩት ወደ ፊት የሚመጡበት ነው” በሚለው መሠረት “ትጉህ ባርያ” የነበሩት አቶ ሬድዋን የአቶ በረከት ስምዖን ቦታ ያዙ ተብሎ ። የሬድዋንም የተስፋ ምድር ይህች ነበረች። የአቶ በረከትን ቦታ ማግኘት
አቶ ሬድዋንን ኢሕአዴግ ግንባር ቀደም የምርጫ ተከራካሪ አድርጎ ለማምጣት በፓርቲው ውስጥ በዚሁ ታሪካቸው የተነሳ የሐሳብ ልዩነት እንደነበር ይነገራል። “ድሮ ይቃወመን በነበረ ሰው መወከል!” በሚል። ዋናው ነገር ሬድዋን ሥራቸውን አይዘነጉም። “የተለያዩ ማኅበራትን ታደራጃለህ”፤ “ከጀርባ ትቆጣጠራለህ”፤ የሚለው የፖለቲካ ቅኝት እየተሰጣቸው ለሚፈልገው ዓላማ ይሰናዳሉ። አቶ ሬድዋንም ይህችን አሠራር ከአዲስ አባባ የክፍለ ከተማ ስበሰባዎች፣ በፍቼ እና በአላጌ ተግብረዋታል። የአዲሱ በረከት ጠንካራ ጎኑም ይህ ነው።
እነ አቶ ሕላዌ መሠረቱን የጣሉለትን ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ የሚወስድ ግንባር ቀደም ካድሬ ይፈለግ ነበር። ኢሕአዴግ ዐይኑን ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ጣለ። ደቡብ ኢትዮጵያ በፖለቲካ እና ሕዝብ አደረጃጀት “የተካኑ” የሚባሉ ሰዎችን ማፍራት ይዟል። አቶ ኀይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ካሊድ አሕመድ፣ ሬድዋን ሁሴን፣ መኩሪያ ኀይሌ ከሌሎቹ አጋር የኢሕአዴግ ፓርቲዎች በላቀ ጎላ ብለው መታየት ጀምረዋል።
በወቅቱ የደቡብ ክልል የትምህርት ቢሮ ሐላፊ፣ የደኢሕዴን ኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ ሬድዋን ሑሴን ደግሞ በተናጋሪነታቸው ይታወቃሉ። በዚያ ላይ የሕዝብ አደረጃጀት ልምድ አላቸው። የሁሉም ዐይን ሰውየው ላይ አረፈ። ሬድዋንም ወደ አዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ሐላፊነት ተመደቡ፡፡
ሥራው ቀላል እና ግልጽ ነው። “ፓርቲውን በሕዝብ ውስጥ ማሥረጽ።” “ከፍተኛ ቁጥር ያለው አባል መመልመል፤ የተመለመሉትንም ከእምነታቸው እንዳይናወጹ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን ማስረጽ – ሁለተኛ ተፈጥሯቸው እስኪመስል። ” በከተማው አስተዳደር ውስጥ የፓርቲ ሥራ ከመንግሥት ሥራ ጋራ የጨው እና የውኃ ያህል እስኪወሃዱ ድረስ ሬድዋን እረፍት የላቸውም። የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራጅተው የፓርቲውን ጥቅም በዘላቂነት እንዲያስከብሩ ይታትራሉ። ሬድዋን በሚመሩት የአዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ሥር የሚገኙ አራት ወሳኝ የመመልመያ እና መከታተያ መዋቅሮችን ይመራሉ። የአባላት ሥልጠና፣ አነስተኛ እና ጥቃቅን እና ትምህርት፣ ግብር መልስ እና ሱፐርቪዥን እና የሕዝብ አደረጃጀት ናቸው።
ሁኔ አቢሲኒያዊ
ኦክስፎርድ ዩ.ኬ
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar