በግልፅ ከተቀመጠው አላማዬ ውጪ ሌላ የተደበቀ አላማ እስከሌለኝ የትም ቦታ ንፁህ አዕምሮ አለኝ ፡፡ንፁህ አዕምር ይዤ እኖራለሁ የመጨረሻው አማራጭ ወደ እስር ቤት መወርወር ሊሆን ይችላል እድል ፈንታችን ይሔ ሊሆን ይችላል ፡፡ይሔ ለኛ የተለየ አዲስ ነገር አይደለም በሰው ሁሉ ላይ ከደረሰው በእናንተ ላይ የደረሰ ምንም ነገር የለም ይላልና መፅሀፍ እኔም የተለየ ነገር ሊደርስብኝ አይችልም ፡፡ከቀድሞም ጀምሮ ኢትዮጵያ እንደዚህ ልጆቿን ስትበላ የኖረች ሀገር ናት፡፡አባቶቻችንም በተረት ይሉታል‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ››እንስራ ለዚች ሀገር ባልን እንደዚህ አይነት ፈተናና መከራዎች መጋረጣቸው ያሳዝናል፡፡ቢያንስ ትውልዱ እንደዚህ አይነት ፈተና እንዳይገጥመው፤ልጄ እንዲህ አይነት ፈተና እንዳይገጥማት እኔ ይህንን ፈተና ተጋፍጬ ማለፍ አለብኝ፡፡ግን ሁሌም ዲሞክራሲያዊ መሆን አለብኝ ብዬ አምናለሁ ፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነ አስተሳሰብን በፀረ ዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት አይቻልም፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነን አስተሳሰብ መፍታት የሚቻለው በዲሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ ነው፡፡በዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ደግሞ ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡
tirsdag 25. november 2014
mandag 24. november 2014
“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን” “ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”

“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- መታሰርህን ለቤተሰብ ተናግረሀል?
ወጣት ተስፋዬ:- ለማንም ሰው እንድናገር አልፈቀዱልኝም፤ መስሪያ ቤቴ አልጠየቀኝም፣ ደሃዋ እናቴ ያለችው ናዝሬት ነው እሷም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ አባቴ አቶ ተካልኝ አስተማሪ ነበር አርባ ጉጉ ላይ ነው በ1985 ዓ.ም በነበረው ግጭት ነው የተገደለው፡፡ ማንም ሳይጠይቀኝ፣ፍ/ቤት ሳልቀርብ 23 ወር ታሰርኩ ልብስ ምግብም የሚያመጣልኝ ሰው አልነበረም፡፡ እናቴም መታሰሬን እንኳ አታውቅም መስሪያ ቤቴም ስኮላርሽፕ አግኝቷል፤ ወደ ውጪ ሃገር ሊማር ሊሄድ ነው የሚባል ነገር ስለነበረ አልጠየቁኝም፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የት ነበር ስኮላርሺፕ ያገኘኸው?
ወጣት ተስፋዬ:- የዛሬ 2 ዓመት አካባቢ የራስመስ ሙንደስን ስኮላርሽፕ አግኝቼ ነበር፡፡ ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ካሊፎርኒያና ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ቶክዮ ባሉ ምሁራን ሪኮመንድ ተደርጌ በጣሊያኑ ፌራሪ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ እንደተፈታሁ ሄጄ ስጠይቃቸው ብዙዎቹ ጓደኞቼ በጣም ደነገጡ፡፡ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ቅማል ተወርሬ … ባካችሁ ተውኝ … ምንም የሌለ ነገር የለም በጣም ተጎድቻለሁ፡፡ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ እናቴ ጋ ስሄድ በጣም ደነገጠች፣ በሕይወት ያለሁ አልመሰላትም 23 ወር ሙሉ ከቤተሰብ ስለተለየሁ ግራተጋባች፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- በእስር ወቅት የደረሰብህ ድብደባና ማሰቃየት ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ በኤሌክትሪክ ጀርባዬ ላይ አቃጥለውኛል፣ በብልቴ ላይና በኩላሊቴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ስላደረሱብኝ ሽንት ችዬ አልሸናም፣ ሽንቴን መቆጣጠርም አልችልም፡፡ ኩላሊቴንም በጣም ያመኛል፡፡ ውሃ ውስጥ እየነከሩ በጣም ደብድበውኛል፡፡ አሁን ስናገር ያመኛል ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደው ስታስበው ለእስር ያበቃህ ወይም ከመንግስት ጋር ያጋጨህ አጋጣሚ ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- መስሪያ ቤቴ ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ነበሩ፤ በጣም ይከታተሉኛል፡፡ በቢ.ፒ.አር ላይ ስብሰባ በተደጋጋሚ ይጠራ ነበር፡፡ እኔም ሠራተኛ ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ነገሮች ሲመጡ እኔ አልቀበልም በግልፅ እናገር ነበር፤ ሠራተኛውም እኔን ይደግፋል፡፡ ከመታሰሬ ጥቂት ጊዜ በፊት ገነት ሆቴል ስብሰባ ነበረን፡፡ በዛ ስብሰባ ላይ በጣም ተከራከርኩ፤ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አቶ ፀጋዬ ማሞ የሚባሉ አሰልጣኝ፣ ከውጭ ጉዳይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና ከንግድና ኢንዱስትሪም የመጡ ነበሩ ስማቸውን የማላስታውሳቸው ባለስልጣን ነበሩ፤ እዛ ላይ ሀሳብ አንስቼ ተከራክሬ ነበር፡፡ “የሠራተኛን ሀሳብ ዳይቨርት ያደርጋል” ይሉኝ ነበር፡፡ መቼም ግን ሀሳቤን በመናገሬ ይህን የመሰለ ስቃይ ይደርስብኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ “አሸባሪ፣ ግንቦት ሰባት” እያሉ እኔ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ፍርድ ቤት ሳልቀርብ ያለምንም ፍርድ በርሜል ውስጥ ውሃ ጨምረው እያስተኙ አሰቃዩኝ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደዚህ ያሰቃዩህ ምን አይነት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ ነው?
ወጣት ተስፋዬ:- እኔን ጥፋተኛ የሚያስደርግ ምንም መረጃ አላገኙም፣ እኔን አስረው ወደ መስሪያ ቤት በተደጋጋሚ ይደውሉ እንደነበር ይነግሩኝ ነበር፡፡ የኢሜይል አድሬሴንም ተቀብለው በርብረዋል ግን ምንም አላገኙም፡፡ እኔ ከማንም ጋር ሊንክ የለኝም ኢሜሌ ላይ የስኮላርሺፕ መልዕክት ካልሆነ በስተቀር ምንም የለውም፡፡ በመስሪያ ቤቴ ሪሰርቸር ነበርኩ፣ በሶሲዮሎጂ ነው የተመረኩት፡፡ ሉሲ የተገኘችበት ሣይት ላይ አፋር፣ ጋምቤላ ብዙ ሳይቶች ሰርቻለሁ፡፡ ከአለቆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሰላማዊ ነው እነሱ ናቸው ስኮላርሽፕ ሪኮመንድ ያደረጉኝ፡፡ አንደኛው ፕሮፌሰር 25 ዓመት ሙሉ እዚህ አገር ሰርቷል፣ አርዲን ያገኘው እሱ ነው፡፡ ሄነሪ ጊልበርት ይባላል፤ እሱም ሪኮመንድ አድርጎኛል፡፡ እኔ በጣም የሚቆጨኝ ደሃዋ እናቴ አረቄና ጠላ ሸጣ ነው ያስተማረችኝ ምን ብዬ ልንገራት እንደዚህ አትጠብቀኝም ከበደኝ፣ አሁን እሷ የምትሰጠኝ ምግብ ራሱ ደምደም አለኝ… (ረጅም ለቅሶ)፡፡ ልጄ በደህናው አይደለም የጠፋው ሞቷል ወይም መኪና ገጭቶታል ብላ ነበር የምታስበው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የከመታሰርህ በፊት ፖለቲካ ተሳትፎ ነበረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- 1997 ዓ.ም የቅንጅት ደጋፊ ነበርኩ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ በ97 የነበረው ሁኔታ ስንት ሰው አለቀ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነበር ታውቃላችሁ ምንም የምናደርገው ነገር አልነበረም ፡፡ በምርጫ አሸንፎ ሥልጣን መያዝ እንደማይቻል ተረዳሁኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም በኋላ የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አልሆንኩም፡፡ ከዚህ በኋላ ከምንም ነገር የተገለልኩ ሆኛለሁ፡፡ አንድ ብርጭቆ ሳትሰብር አሸባሪ ስትባል አስብ እንግዲህ አንድ ብርጭቆ እንኳን ሰብሬ አላውቅም ባለኝ እውቀት እንደውም ለእውቀት ነው የምጓጓው እውቀቴን አሳድጌ አገሬን ለመለወጥ ነው የማስበው እኔን ምንም የሚመለከተኝ ነገር የለም አሸባሪም ግንቦት ሰባትም አይደለሁም፡፡ስትደበደብ፣ ስትሰቃይ ያላደረከውን አድርጌያለሁ ትላለህ፤ በርሜል ውሃ ሞልተው ይከቱሃል ያሰቃዩሃል፡፡ አያሳዝንም ይሄ? እንዴት አድርጎ እዚህ አገር ይኖራል? 23 ወር ሙሉ አስረው ማሰቃየታቸው ሳያንስ የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል፡፡ እኔ ግን ከዚህ በላይ ሞት የለም ብዬ ነው የነገርኳችሁ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- አሁን የት ነው የምትኖረው?
ወጣት ተስፋዬ:- መኖሪያ የለኝም … (ረጅም ለቅሶ)
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝን ለመርዳት የምትፈልጉ አንባብያን ከፍኖተ ነፃነት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (ምንጭ ፍኖተ ነጻነት)
በፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ ዋና አቀናባሪው ተስፋዬ ገ/አብ መሆኑን ያውቃሉ? (ሊያነቡት የሚገባ) (በአለማየሁ መሰለ )

ለዛሬ የማቀርበው መረጃ ተስፋዬ ገብረአብ እንደ ሸፋን ከሚጠቀምበት የደራሲነት እናየጋዜጠኘነት ስራ ባሻገር ለማመን በሚያዳግት ይሰራ የነበረውን የወንጀል ድርጊት ፍንትው አድርጎ ያሳያል።ከዚህ በታች አባሪ ተደርጎ የተያያዘው በእጅ የተጻፈ መረጃ፣በእጄ ላይ ካሉ መረጃዎች መሃከልትኩረቴን የሳበው ነው።እንደምትመለከቱት በራሱ በተስፋዬ ገብረአብእጅየተጻፈነው።ከሌሎችመረጃዎች ለየት የሚያደርገው ደግሞ፣እንደሌሎች መረጃዎች በፎቶኮፒ እጄ ላይ የቀረሳይሆን፣ዋናው(ኦርጅናል)መሆኑ ነው። ምክንያቱም በቀጥታ ወንጀል የተጻፈበት ሆኖ ስለታየኝ ነው።ከእጅጽሁፉ ላይ እንደምትመለከቱት፣መኩሪያ መካሻ ከተባለ ግለሰብ ጋር ድብቅ(ህቡእ) ስራ ለመስራትጀምረው ነበር።እንደኔ ግምት የኤርትራ መንግስትን ጥቅም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስፈጽማልብለው ያሰቡትን ተልእኮ ለመፈጸም አሲረው ነበር፡፡እንደ መረጃው ከሆነ መኩሪያ መካሻ የተባለውግለሰብ ከፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ በኋላ ፈርቶ ይሁን ሌላ ባይታወቅም፣ከተስፋዬ ጋር ያለውን
ግንኙነት አቋርጧል።የፒያሳው የቦንብ ፋንዳታ ብሎ የተገለጸው ደግሞ ሌላ ሳይሆን በ2002 እኤአበትግራይ ሆቴል ላይ የደረሰው ፍንዳታ ነው።የእጅ ጽሁፉን ሙሉ ይዘትና ለአንባቢ ይመች ዘንድ የተየብኩትን ይመሳከር ዘንድ እንደሚከተለው
አቅርቤዋለሁ።አሰሪ መሆንና በቀጥታ ከእሳቱ ጋር መጋፈጥ ልዩነት አላቸው መኩሪያ መካሻ የተባለው ሰው ጥሩ ጀምሮነበረ።ፒያሳ ላይ ቦምብ ሲፈነዳ ከእኔ ጋራ ያለንን ግንኙነት አቁዋረጠ።በጣም ጉዋደኛየ ነበር ለስራውስል ሰዋሁት። ጉዋደኛንመሰዋቴ ትልቅ ነገር አይደለም።ህይወታቸውን የሰዉ፣ክቡር ዜጎች ያሉበት ሃገርሰው ነኘና። እዚህ ላይ በትክክል ማሰብ እችላለሁ።አስቃቂውን ስሜቴን ግን ለመግለጽ ያህል ነው።ያሸማቅቁሃል ሲሳካልኝ በደስታ መጠጣት፣ሲከሽፍብኝ በንዴት መጠጣት፣ልምድ አደረግኩት።ደረጀደስታ እራሱ ከገፋፋኝ በሁዋላ መልሶ በኢትኦጵያ የማምን ኢትዬጵያዊ ነኝ ሲለኝ ምን እንደሚሰማገምቱት።
ሚኒስትር የነበረው ደስታ ወልደማርያም ጋር ለዘላለሙ ተለያይቻለሁ።እነዚህ ሰዎች ለወያኔ ነግረው ምንያስፈጽሙብኝ ይሆን የሚል ስጋት አለብኝ።ያድዋን ወረዳ ያበላሸው ………… የደረሰበትን ታሪክእያሰብኩ መሰቃየቴን አልተውኩም።ከብብቱፈልቅቄ ካስቀረዋቸው መረጃዎች ከዚህ በታች እንደምታዩት በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ላይየኢትዬኤርትራ ጦርነት በሁዋላ እሱም እንዳለቆቹ እንዳቄመ ነው የምናየው።እስከጦርነቱ መጀመሪያ ድረስግን፣የህወሃት አባልነቱን ግዴታ ለመወጣት በአለቆቹ ታዞ ይሁን በራሱ ተነሳሽነት የአማራንና የኦሮሞንህዝብ ለማጋጨት ነበር ስራዬ ብሎ የተያያዘው።አሁን ደግሞ በኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤትፕሮጀክት ተቀርጾለት የትግራይ ህዝብንም የትኩረታቸው መነሻና መድረሻ አካተው በተቀረው የኢትዬጵያህዝብ ለማስጠላትና ለማሸማቀቅ፣የተስፋዬ ገብረአብን ብእር እንደዋነኛ መሳሪያ እየተጠሙበት እንደሆነበግልጽ ማየት ይቻላል።ከላይ እንደገለጽኩት መስሪያ ቤቱ በሃገራችን ህዝቦች መሃል ያለውን መተማመን እና አንድነት ለማትፋትፕሮጀክት ተቀርጽለት ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በዚህ ግለሰብ ኣማካኝነት እየተፈፀመ የከረመው እና
ሊፈፀም እየቴሰረ ያለው ሤራ እንደሚከተለው ይሆናል፥፥አጠቃላይ የግቡ አላማ የኢትዮጵያን አንድነት ማዳከም ነው፥፥ ስልታዊ አካሄዳቸው ድግሞ አንዱንብሄረሰብ ከሌላኛው ጋር እርስ በእርስ እንዳይማመኑ በማድረግ በመሃላችን አንድ ሃገራዊ አጀንዳና እሴትእንዳይኖረን ማድረግ ነው፥፥
ለዚህ ማጠናከሪያ የሚሆነው፣የአማራ፣የኦሮሞ እና የትግራይ ብሄረሰቦችን ለምሳሌ ያህል ብንወስድአንድ የኦሮሞ የዘር ሃረግ ያለው ግለሰብ፣አማራ ከሆነ ግለሰብ ጋር አብረው በጓደኝነት፣በጋብቻሊኖሩ የሚችሉበት የግኑኝነታችው መሰረት አንድና አንድ ብቻ እንዲሆን ነው የሚፈለገው፡፡ ያምየትግሬ ጥላቻ ነው።በተቀረው ሁለቱ ግለሰቦች የጋራ የሆነ ሃገራዊ አጀንዳ እና እሴት ቀርጸውስለዲሞክራሲ፣ፍትህ፣ልማትና የሰብአዊ መብት መከበር እንዲሁም ሌሎች ሃገራዊ አጀንዳዎች
እንዲያግባቧቸው ፈጽሞ አይፈለግም።የወዳጅነታቸው መሰረት አንድ ብቻ እንዲሆን ነውየሚፈለገው፣እርሱም የትግሬ ጥላቻ ብቻ ነው። በሌላኛውም መአዘን የትግራይና ኦሮሞ ብሄርተወላጆች የወዳጅነታቸውና ያብሮነታቸው መሰረት መሆን ያለበት፣የአማራ ጥላቻ ብቻ እንዲሆንነው እቅድ ወጥቶለት ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት በተግባር ላይ እንዲውል እየተደረገ ያለው።ይህንን ለምሳሌ አነሳን እንጂ ሁሉም የሃገራችን ብሄሮች በተገኘው አጋጣሚና እድል በዚህ መልክበጎሪጥ እንዲተያዩ በማድረግ እንደሰው ወይንም እንደ ኢትዬጵያዊ ማሰብ አቁመን ሳንፈልግበመረጥነው የብሄር ማንነታችን ላይ አትኩረን ስንኩላን እንድንሆን የተሸረበ ሴራ አካል ነው።እዚህጋ በኤርትራ የደህንነትና መረጃ መስሪያቤት ሙሉ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በመታገዝ
የተስፋዬ ስነ-ጽሁፍ የበኩሉን የማናከስ ሚና በመጫወት ሃገራችንን ወደማያባራ ጦርነትና እልቂትለመክተት የራሱን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።ሁለት አመት ለሚቆጠር ጊዜ ቤቴ አስጠግቸው ሲኖር ከሚያደርጋቸው የስልክ ልውውጦች
እንደተረዳሁት ከሆነ በተስፋየ ገብረአብ ስም ይወጡ የነበሩ ጽሁፎች በአብዛኛው ማለት ይቻላልከኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የፕሮፓጋንዳ መልእክቶች እንደነበሩ ህያው ምስክር ነኝ።ይህ ማለት ተስፋየ በጋዜጠኝነት ወይንም በደራሲነት ሽፋን የመረጃ መስሪያቤቱ የፕሮፓጋንዳማስተላለፊያ መሳሪያ በመሆን ለኤርትራን ብሄራዊ ጥቅም የሚውል ስራ ይሰራ የነበረ መሆኑን
አስረጂ ነው።ለምሳሌ ከደህንነት መስሪያቤት የላኩለትን ምንም ለውጥ እንዲደረግበት ሃሳብሲያቀርብ፣እነሱም ሃሳቡን ሳይቀበሉት ሲቀሩ በር ዘግቶ በስልክ ሲጨቃጨቅና ሃሳቡ ሲሸነፍበተደጋጋሚ መስማቴን አስታውሳለሁ።እንደ እኔ እምነት ከሆነ ራሱ የኢትዬጵያ መንግስት እያራመደ ያለው የተንሸዋረረና የከረረ የዘርማንነትን ብቻ ማእከል ያደረግ የፖለቲካ ስርአት፣ከውጪ ሊመጣ ለሚችል እንዲህ አይነትየማጋጫት ወይንም ሃገር የማፍረስ ጣልቃገብነት በር እንደሚከፍት ለመተንበይ አዳጋች አይሆንም።ወደ ነጥቤ ልመለስና ከላይ በጠቀስኩት መሰረት፣አማራን ከተለያዩ የሃገሪቱ ብሄሮች ጋር እንዴትሲያላትምእንደነበረ፣ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ጋር በክፍል አንድ ሪፖርታችን ላይ በሰፊውሄደንበታልና አሁን አልመለስበትም። ከዚህ በታች ደግሞ የትግራይ ብሄር አባል በሆኑ ግለሰቦች ላይማህበራዊ ፤ የስነልቦና የአካል ጥቃት መፈጸሙ፤ የሱ መጽሃፍ ስኬት ውጤት እንደሆነ ለኤርትራየመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የቅርብ ተጠሪው ለሆኑት አቶ ዓለም እንዲህ በማለት በጽሁፍየፋክስ መልእክት ረቂቅ (ድራፍት ) ያስተላልፍ እንደነበረ መረዳት እንችላለን፡
torsdag 20. november 2014
መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን ያጣል

የአሜሪካ ባርያ ፈንጋዮች ትናንት በገፍ ከአፍሪካ በባርነት ያመጡዋቸው አፍሪካውያን አንድ ቀን በአንድ ቆመውና በህብረታቸው ጠንክረው ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት እንዳይነሱ ሀ ብለው የነጠቋቸው ማንነታቸውን፤ ታሪካቸውንና መገኛቸውን ነበር፡፡ እንደ እቅዳቸውም እነሆ ዛሬ አብዛኛው ጥቁር አሜሪካዊ እኔ ማን ነኝ? መምጫዬስ ከወደየት ነው? በሚሉና በመሳሰሉ ጥያቄዎች ተተብትቦ ለምላሹ ሲውተረተር መገኘቱ፤ እንዲሁም ዛሬም ከተገዢነት መንፈስ ራሱን አላቆ በሁለት እግሩ ለመቆም ሲታትር ይገኛል፡፡
ሌላው የኢጣልያ ወራሪን ሀይል ቅስም የሰበረውና በአለም አቀፍ ደረጃ ቅሌት ያከናነበው የአድዋ ጦርነት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ቅሌት በደም አጥቦ ሀያልነቱን ለአለም ለማሳየት በሞከረበት ሁለተኛው ወረራ ወቅት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የአድዋ ጦርነት የመሩት የአፄ ሚንሊክ ሀውልትን ከጥልቅ ጉድጓድ መቅበር እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ባጠቃላይ አንድ ህዝብ እንደ ህዝብና ሀገር ጠንክሮና በነፃነት ኮርቶ ለመኖር ብሎም ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር መቻል ከማረጋገጫው አንዱ የትናንት ማንነቱና የመገኛ ታሪኩ መሆኑን ከላይ በምሳሌነት ያነሳናቸው ነጥቦች ያረጋግጣሉ፡፡
ታሪክ ለአንድ ህዝብ የማንነቱ መገኛ፤ የመገኛው ምንጩና መምጫውን የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የነገ መዳረሻውን የመመልከቻ መነፅርና ጠንክሮ የመንቀሳቀሻው ጉልበቱ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ መሳሪያ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ አንድ ህዝብ ታሪኩ ከጠፋ ሊገጥመው የሚችለው ችግርና ፈተና እንዲህ በቀላሉ የሚገመት ያለመሆኑንና እንደ ህዝብ እንደ ሀገር ቀጣይነቱን በቀላሉ መፍትሄ ከማይገኝለት ፈተና ውስጥ ይከተዋል ማለት ነው፡፡
ኢትዮጵያችን ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ህልውናዋ አደጋ ላይ የወደቀበት መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ባለፉት 23 አመታት በዘረኞቹ የወያኔ ጉጅሌዎች እጅ ከወደቀችበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ የታሪካችንና የባህልችን ዋና ዋና እሴቶች ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚና በግልፅ ከወያኔው መሪ እስከ ተራ ደጋፊው የሚወረወረው በትር ያረጋግጣል፡፡ ጉጅሌዎቹ የነፃነት ምልክት የሆነውንና በዕልፍ አዕላፋት ደም መሥዋዕትነት ፀንቶ የቆየውን ሰንደቅ ዓላማ በሶ መጠቅለያ ጨርቅ ከማድረግ ጀምረው ዛሬ በምሁራን ጥረትና በእያንዳንዱ ዜጋ ድጋፍ የተሰባሰቡት የታሪኮቻችን መዛግብት በጥንቃቄ ከተቀመጡበት (ቤተ-መዛግብት) እያወጡ ከማውደምና ለስኳር መጠቅለያነት እስከ መሸጥ ደርሰዋል፡፡
ታሪካዊ ገዳማት ፈርሰዋል፤ ታሪካዊ ቅርሶች ለባእዳን አልፈው ተሽጠዋል፤ የነፃነት ታሪካችን እየተደለዘ በወያኔያዊ ዘረኛ የፈጠራ ታሪክ መተካቱ ቀጥሏል፤ ታሪካዊ ጀግኖቻችንን ማዋረድና ማውገዝ የእለት ተእለት ስራቸው ሁኗል። ወ ያኔዎች ኢትዮጵያዊነት ቅዝት ሆኖባቸዋል፤ ስለዚህም ቀንደኛ ጠላታቸው አድርገው ፈርጀውታል፡፡ ይህ የዘረኝነትና የዘረፋ ስርዓታቸው ውሎ ማደር የሚረጋገጠው ኢትዮጵያዊነት መመታት ሲችል ብቻ ነው ብለውም በፅኑ ያምናሉ፡፡ ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊነታችንን ሊያዳክም ብሎም ሊያጠፋ ይችላል ብለው የገመቱትን ሁሉ ከመፈፀም የማይመለሱት፡፡ ለዚህም ነው በስንት ጥረትና በብዙዎች ድካም ተሰባስቦና ተደራጅቶ የቆየውን የታሪክ መዛግብትና መፅሀፍት ከቤተ-መዘክር አውጥቶ በኪሎ ለመቸብቸብ የበቁት፡፡
ታዲያ ኢትዮጵዊ ነን የምንል ሁሉ ዘሬም እንደትናንቱ ይህን በማንነታችን ላይ የሚደረግ የጥፋት ዘመቻ ለማስቆም መነሳት ግድ ይለናል። እየተፈፀመ ያለው የታሪክ ማጥፋት ዘመቻ ለነፃነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ከምናደርገው ትግል እኩል ጎን ለጎን ለታሪካዊ ቅርሶቻችንና መዛግብቶቻችን ከጥፋት የመከላከልና የማዳን ስራ የመስራት የትውልድ ኃላፊነት አለብን፡፡ አለበለዚያ መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን አያውቅምና የምናደርገው የነፃነት ትግል የተሟላ ውጤት ማስገኘቱ ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አይቀሬ መሆኑን መገንዘብ ይገባናል፡፡ ተገንዝበንም ወያኔን በቃህ ልንለው ይገባል፡፡
በመጨረሻም ጂኦርጅ ኦርዌል ‘The most effective way to destroy people is to deny and obliterate their understanding of their own history” ብሎ ጽፎ ነበር። ህወሃቶች የዚህ ፍልስፍና ተከታዮች መሆንን በመምረጥ ለራሳቸው ውረደትን ፤ለአገራቸውም ውደቀትን ተመኝተዋል። ኢትዮጵያችን መንግስት በጠላትነት ተሰልፎ ከአገራችን ከህዝብና ለአገሪቷ እሴቶች ጋር የሚዋጋበት አገር ሁናለች። ህወሃት በብዙ መልኩ ሲታይ የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላት መሆንን የመረጠ ቡድን ነው። የህወሃት በኢትዮጵያ ላይ በጠላትነት መቆሙ ያስቆጣቸው ወጣቶች እምቢ ለአገሬ፤ እምቢ ለክብሬ ብለው ተነስተው ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ተሠማርተዋል።ግዜው ከእነዚህ ወጣቶች ጎን የምንቆምበትም ጭምር ነውና ተነሱና ለነፃነታችንና ለአገራችን ዝና ለህዝባችን ክብር አብረን ታግለን ጠላትን የመረጠውን ህወሃትን እናስወግድ እና ንፁህ አገር እንፍጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!
የማንዴላን ጽዋ የተጎነጨው ሃብታሙ አያሌው (በዳዊት ሰለሞን
በ1972 የበጋ ወራት ኔልሰን ማንዴላ ከ27 ዓመት የእስር ፍርዱ 18ቱን ዓመት ወደሚያሳልፍበት ሮቢን ደሴት መጣ፡፡ጠባብ በሆነች ክፍሉ ወለሉ መኝታው፣ መጸዳጃው ደግሞ ቅርጫት ነበረች፡፡ ከባድ ስራ እንዲሰራም ይገደድ ነበር፡፡በዓመት ውስጥ ለ30 ደቂቃ እንዲጎበኘው የሚፈቀድለት ለአንድ ሰው ብቻ ነበር፡፡ በየስድስት ወራቱ አንድ ደብዳቤ እንዲቀበልና እንዲጽፍ ይፈቀድለት ነበር፡፡››
ሐብታሙ አያሌው ደቡብ አፍሪካ ያስተናገደችውን የዓለም ዋንጫ ለመመልከት ወደ አገሪቱ ባቀናበት አጋጣሚ ከልቡ የሚያደንቃቸው ኔልሰን ማንዴላ ለ18 ዓመታት የታሰሩባትን ታሪካዊዋን ክፍል በመጎብኘት የመታሰቢያ ፎቶ ግራፍ ተነስቶ ነበር፡፡
የጸረ አፓርታይድ ትግል እንዲቀጣጠልና ጥቆሮች በገዛ አገራቸው ባይተዋር የሚሆኑበት የነጮች አገዛዝ እንዲያከትም ኢትዮጵያ ድረስ መጥቶ ወታደራዊ ስልጠና የወሰደው ማንዴላ በሮቢን አይስላንድ ከዓለም ተነጥሎ እንዲቀር ብዙ መከራ ተቀብሏል፡፡
ወጣቱ ሐብታሙ በአእምሮው ይህንን እያሰላሰለ የነጻነት መንገድ ውጣ ውረድ እየታየው ገጽታውን ለካሜራ ባለሞያ የሰጠ ይመስለኛል፡፡ሐብታሙ በዚያን ወቅት የበሰለ እንጀራ ሌሎች ጋግረው እርሱ እንዲበላ ብቻ የሚጠበቅ ሰው ነበር፡፡
ልክ ሙሴ በፈርኦን ቤት አድጎ የፈርኦን ልጅ መባልን በመጠየፍ የተራ ሰው ህይወት መምራት እንደጀመረ ሐብታሙም ሮቢንን የጎበኘው ‹‹ኢህአዴግ የጋገረውን እንጀራ ከመብላት ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኝ የዘመናችን ሮቢን (ማዕከላዊ) መታሰርን እየመረጠ ነበር፡፡
ሐብታሙ ከደቡብ አፍሪካ መልስ ‹‹አንድነታችን ከልዮነታችን በላይ ነው›› በሚል መሪ ቃል ‹‹አንድነት›› የሚል ቃልና ስም አምርሮ ከሚጠየፈው ኢህአዴግ ጋር ትግል ጀመረ፡፡
ሮቢንን የጎበኘው ሐብታሙ የማንዴላ መንፈስ ተጠናውቶት የኢትዮጵያ ፖለቲካ መፍትሄ ፍቅር፣መቻቻልና ብሄራዊ እርቅ ማድረግ መሆኑን መስበክ ቀጠለ፡፡
ይህ ለኢህአዴግ ተንበርካኪነት፣የኒኦ ሊበራሊዝም አቀንቃኝነትና የነፍጠኞች አካሄድ ነው፡፡ ሐብታሙም ጥርስ ውስጥ ገባ፡፡ ‹‹ኢህአዴግ ከታሪክ ይማር›› የሚለው ውትወታው ጆሮ አለማግኘቱ ይታወቅ ዘንድም በአንድ ማለዳ ብሶት የወለዳቸው ነፍጥ አንጋቾች ሐብታሙን መሬት ላይ አስተኝተው እየጎተቱት ማዕከላዊ (ሮቢን) አስገቡት፡፡
ሐብታሙ በኢትዮጵያው ሮቢን ቅዝቃዜው አጥንት ሰብሮ በሚገባ ክፍል ውስጥ ታስሯል፣ መኝታው ወለሉ ናት፤ ለወራት ቤተሰቦቹን እንዳያገኝ ጠበቃውም እንዳይጎበኙት ተደርጓል፣ ድብደባ ተፈጽሞበታል፣ ህክምና እንዳያገኝ ተደርጓል፣ ያልፈጸመውን ነገር እንደፈጸመ በማድረግ ቃሉን እንዲሰጥ ተገድዷል፣ክፍሉ በጨለማ የተዋጠች ከመሆኗም በላይ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዳይገናኝ ተወስኖበታል፡፡
የማንዴላ መንገድ በኢትዮጵያ ተመሳሳዩን ጽዋ እንደሚያስጎነጨው ተገንዝቧል፡፡ እናም ጽዋዋን ለመጠጣት የማንዴላ መንፈስ እንዲረዳው ጸሎት አድርጓል፡፡
But Robben Island became the crucible which transformed him. Through his intelligence, charm and dignified defiance, Mandela eventually bent even the most brutal prison officials to his will, assumed leadership over his jailed comrades and became the master of his own prison. He emerged from it the mature leader who would fight and win the great political battles that would create a new democratic South Africa.
በሮቢን ደሴት የብረት ግግር የተቆለፈበት ማንዴላ በዚያ የሚገኙ አረመኔ የእስር ቤት ሃላፊዎችን ልብ በማሸነፍ በሳል መሪ ሆኖ እንደወጣ ሁሉ ሮቢንን የጎበኘውና በኢትዮጵያው ሮቢን (ማዕከላዊ) የሚገኘው ሐብታሙም በዚሁ መንፈስና ጥንካሬ እንደሚወጣ እምነታችን ጽኑ ነው፡፡
ሐብታሙ አያሌው ደቡብ አፍሪካ ያስተናገደችውን የዓለም ዋንጫ ለመመልከት ወደ አገሪቱ ባቀናበት አጋጣሚ ከልቡ የሚያደንቃቸው ኔልሰን ማንዴላ ለ18 ዓመታት የታሰሩባትን ታሪካዊዋን ክፍል በመጎብኘት የመታሰቢያ ፎቶ ግራፍ ተነስቶ ነበር፡፡
የጸረ አፓርታይድ ትግል እንዲቀጣጠልና ጥቆሮች በገዛ አገራቸው ባይተዋር የሚሆኑበት የነጮች አገዛዝ እንዲያከትም ኢትዮጵያ ድረስ መጥቶ ወታደራዊ ስልጠና የወሰደው ማንዴላ በሮቢን አይስላንድ ከዓለም ተነጥሎ እንዲቀር ብዙ መከራ ተቀብሏል፡፡
ወጣቱ ሐብታሙ በአእምሮው ይህንን እያሰላሰለ የነጻነት መንገድ ውጣ ውረድ እየታየው ገጽታውን ለካሜራ ባለሞያ የሰጠ ይመስለኛል፡፡ሐብታሙ በዚያን ወቅት የበሰለ እንጀራ ሌሎች ጋግረው እርሱ እንዲበላ ብቻ የሚጠበቅ ሰው ነበር፡፡
ልክ ሙሴ በፈርኦን ቤት አድጎ የፈርኦን ልጅ መባልን በመጠየፍ የተራ ሰው ህይወት መምራት እንደጀመረ ሐብታሙም ሮቢንን የጎበኘው ‹‹ኢህአዴግ የጋገረውን እንጀራ ከመብላት ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኝ የዘመናችን ሮቢን (ማዕከላዊ) መታሰርን እየመረጠ ነበር፡፡
ሐብታሙ ከደቡብ አፍሪካ መልስ ‹‹አንድነታችን ከልዮነታችን በላይ ነው›› በሚል መሪ ቃል ‹‹አንድነት›› የሚል ቃልና ስም አምርሮ ከሚጠየፈው ኢህአዴግ ጋር ትግል ጀመረ፡፡
ሮቢንን የጎበኘው ሐብታሙ የማንዴላ መንፈስ ተጠናውቶት የኢትዮጵያ ፖለቲካ መፍትሄ ፍቅር፣መቻቻልና ብሄራዊ እርቅ ማድረግ መሆኑን መስበክ ቀጠለ፡፡
ይህ ለኢህአዴግ ተንበርካኪነት፣የኒኦ ሊበራሊዝም አቀንቃኝነትና የነፍጠኞች አካሄድ ነው፡፡ ሐብታሙም ጥርስ ውስጥ ገባ፡፡ ‹‹ኢህአዴግ ከታሪክ ይማር›› የሚለው ውትወታው ጆሮ አለማግኘቱ ይታወቅ ዘንድም በአንድ ማለዳ ብሶት የወለዳቸው ነፍጥ አንጋቾች ሐብታሙን መሬት ላይ አስተኝተው እየጎተቱት ማዕከላዊ (ሮቢን) አስገቡት፡፡
ሐብታሙ በኢትዮጵያው ሮቢን ቅዝቃዜው አጥንት ሰብሮ በሚገባ ክፍል ውስጥ ታስሯል፣ መኝታው ወለሉ ናት፤ ለወራት ቤተሰቦቹን እንዳያገኝ ጠበቃውም እንዳይጎበኙት ተደርጓል፣ ድብደባ ተፈጽሞበታል፣ ህክምና እንዳያገኝ ተደርጓል፣ ያልፈጸመውን ነገር እንደፈጸመ በማድረግ ቃሉን እንዲሰጥ ተገድዷል፣ክፍሉ በጨለማ የተዋጠች ከመሆኗም በላይ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዳይገናኝ ተወስኖበታል፡፡
የማንዴላ መንገድ በኢትዮጵያ ተመሳሳዩን ጽዋ እንደሚያስጎነጨው ተገንዝቧል፡፡ እናም ጽዋዋን ለመጠጣት የማንዴላ መንፈስ እንዲረዳው ጸሎት አድርጓል፡፡
But Robben Island became the crucible which transformed him. Through his intelligence, charm and dignified defiance, Mandela eventually bent even the most brutal prison officials to his will, assumed leadership over his jailed comrades and became the master of his own prison. He emerged from it the mature leader who would fight and win the great political battles that would create a new democratic South Africa.
በሮቢን ደሴት የብረት ግግር የተቆለፈበት ማንዴላ በዚያ የሚገኙ አረመኔ የእስር ቤት ሃላፊዎችን ልብ በማሸነፍ በሳል መሪ ሆኖ እንደወጣ ሁሉ ሮቢንን የጎበኘውና በኢትዮጵያው ሮቢን (ማዕከላዊ) የሚገኘው ሐብታሙም በዚሁ መንፈስና ጥንካሬ እንደሚወጣ እምነታችን ጽኑ ነው፡፡
tirsdag 18. november 2014
ዩጋንዳና የቀጣዩ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ዕጩ ጉዳይ
የዩጋንዳ «ናሽናል ሬዚዝተንስ ሙቭመንት» ፓርቲ ፕሬዚደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒን እአአ ለ2016 ዓም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በዕጩነት ለማቅረብ የያዘው ዕቅድ ብርቱ ክርክር አስነስቷል።

ዮዌሪ ሙሴቬኒ እአአ ከ1986 ዓም ወዲህ በዩጋንዳ የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን እንደያዙ ይገኛሉ። ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ የሀገሪቱን ሕገ መንግሥት በተደጋጋሚ ባማሻሻል ካለፉት 28 ዓመታት ወዲህ ሀገሪቱን መምራታቸውን ቀጥለዋል።
በአንድ ወቅት የአንድ አፍሪቃዊ ሀገር ርዕሰ ብሔር ከአስር ዓመት በላይ በሥልጣን መቆየት የለበትም ሲሉ የተናገሩት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከሥልጣናቸው ለመውረድ ሀሳብ እንደሌላቸው የፖለቲካ ተንታኞች ገልጸዋል። በዩጋንዳ የሚታዩት ሁኔታዎች እንደጠቆሙት፣ በምሕፃሩ «ኤን አርኤም» በመባል የሚታወቀው ገዢው የዩጋንዳ «ናሽናል ሬዚዝተንስ ሙቭመንት» ፓርቲ እአአ በ2016 ዓም በሀገሪቱ ለሚካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ብቸኛው ዕጩ አድርጎ ለማቅረብ እየጣረ ነው። ሙሴቬኒ ለአምስተኛ የሥልጣን ዘመን በዕጩነት እንዲወዳደሩ የተያዘውን ጥረት የተቃወሙ ሶስት የመብት ተሟጋቾች ይህንኑ ተቃውሟቸውን ለምሥራቅ አፍሪቃ የፍትሕ ፍርድ ቤት አቅርበዋል።
rechts<br />
“>
“>
የፖለቲካ ታዛቢዎች እንደታዘቡት በገዢው ፓርቲ ውስጥ የሥልጣን ፉክክሩ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው። ይሁንና፣ እንደ ፖለቲካ ተንታኙ አንጀሎ ኢዛማ ግምት፣ ይኸው ፉክክር ለቀጣዩ ምርጫ ያን ያህል ስጋት የሚፈጥርባቸው አይሆንም።
« ፕሬዚደንቱ ቀጣዩን ምርጫ በተመለከተ እየተከተሉት ያለውን አሰራር ስንመለከት፣ ፉክክሩ ቀላል አለመሆኑን ለመረዳት እንችላለን። በተለያየ ደረጃ፣ ማለትም ከቀድሞ ታጋይ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ዴሞክራሲን ማጠናከር ከሚፈልገው የወጣቱ ትውልድም ፉክክር ገጥሟቸዋል። በቀጣዩ ምርጫ ግን ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ ከገዛ ራሳቸው የ«ኤን አርኤም» ፓርቲም ሆነ በጠቅላላ ከዩጋንዳ የፖለቲካ መድረክ ጠንካራ ተፎካካሪ ሊሆንባቸው የሚችል አንድም ተቀናቃኝ የላቸውም። »
አርያም ተክሌ
fredag 7. november 2014
የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ
ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡
በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

torsdag 6. november 2014
የደህንነት ሃይሎች ዜጎችን እያፈኑ መውሰዱን ቀጥለውበታል
ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተጠናክሮ የቀጠለው የገዢው ፓርቲ አፈና መንግስት ራሱ ያስታጠቃቸውን ታጣቂዎች ትጥቅ እስከማስፈታት መድረሱን ምንጮች ገለጹ
በትግራይና በአማራ ክልሎች ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው አፈና ቀጥሎ ጥቅምት 26 ቀን 2007 ኣም የሰላም ታጋይ እየጠባለ የሚታወቅ ወጣት ሽሻይ አዘናው በመቀሌ ከተማ በትግራይ ክልል የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ገ/ህይወት ካህሳይ እና በደህንነት ሃይሎች ከሚሰራበት የኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት የትግራይ
ክልል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ታስሮ እና ቤቱ ተበርብሮ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዷል። ሽሻይ አዘናዉ የዓረና ትግራይ መስራችና ማእከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረ በቅርቡ ደግሞ ከዓረና ወደ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ የተቀላቀለ ወጣት ነው።
በተመሳሳይ ዜና ደግሞ ቋራ በደላ ቀበሌ አካባቢ መሳሪያ የታጠቁ አርሶአደሮች መሳሪያቸውን እየተነጠቁ ነው። ትክል ድንጋይ አካባቢም እንዲሁ በርካታ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን እንዲያስረክቡ መደረጋቸውን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል።
ባለፉት ሶስት ቀናት በትግራይ ክልል በምዕራባዊያን ዞን ቃፍታ ሁመራ ወረዳ ዳንሻ ከተማ የአረና ፓርቲ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ዘነበ ሲሳይ ጥቅምት 25፣ 2007 ዓም ከቤታቸው ተወስደው ሲታሰሩ፣ እንዲሁም በተመሳሳይ ቀን በሁመራ አረና የቁጥጥር ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አማረ ተወልደ ታስረዋል። ከወራት
በፊት የታሰሩትን አብራሃ ደስታንና አያሌው በየነን ጨምሮ 7 የፓርቲው አመራሮች በእስር ላይ ናቸው። በተመሳሳይ ቀን በአማራ ክልል ምዕ/ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን አበበ እና ሶስት የድርጅቱ አባላት ተይዘው ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ ከ10
ያላነሱ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አንዱአለም አራጌ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ ናትናኤል መኮንንና ሃብታሙ አያሌው አሁንም በእስር ላይ ናቸው።
የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝም እንዲሁ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ሶስት የሰማያዊ ፓርቲ የአርባምንጭ አመራሮች አሁንም ድረስ በእስር ላይ ናቸው።
በምእራብ ጎጃም በፍኖተሰላም ከተማ የመኢአድ የወረዳው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) ሰብሳቢ የሆነው ዘሪሁን ብሬ ረቡዕ ጥቅምት 26፣ 2007 ዓም ተይዞ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስዷል።
tirsdag 4. november 2014
← የአሜሪካ መንግስት የታሰሩ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ ጠየቀ!!

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ለትራንስፖርት ሚኒስቴር ሪፖርት ያቀርባል፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ወርቅነህ ገበየው የመንገድ ባለሥልጣን ቦርድም ሰብሳቢ ናቸው፡፡
ሰሞኑን አቶ ዛይድና አቶ ወርቅነህን የማያግቧቧቸው ነገሮች እየተካረሩ መምጣታቸውን የሚናገሩት ምንጮች፣ አቶ ወርቅነህ የደረሱበት ድምዳሜ ለረዥም ጊዜ የሠሩትን አቶ ዛይድ ከሥልጣናቸው እንዲነሱ ማድረግ ነው፡፡ ከዚህ በላይ በጥልቀት በመሄድ ሁለቱን ባለሥልጣናት ያላግባባው፣ በቅርቡ ለቻይና ኩባንያዎች የተሰጡ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንደሆኑ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ኩባንያዎቹ ከዚህ ቀደም የወሰዱትን የመንገድ ፕሮጀክት ሳያጠናቅቁ ተጨማሪ ሥራ ሊሰጣቸው አይገባም በሚሉ ሐሳቦች ላይ አቶ ወርቅነህና አቶ ዛይድ መግባባት አለመቻላቸው ተጠቅሷል፡፡
አቶ ዛይድ ከ1996 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት አገልግለዋል፡፡ ከአቶ ዛይድ በትምህርታቸው ትራንስፖርት ኢኮኖሚስት ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ መንገድ ልማት ዘርፍ ብዙ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ይነገርላቸዋል፡፡ አቶ ዛይድ ባለሥልጣኑን በተለያዩ ደረጃዎች በኃላፊነት ማገልገላቸውን በቅርብ የሚያውቋቸው ይናገራሉ፡፡
ከባለበጀት መሥሪያ ቤቶች ትልቁ የበጀት ተጠቃሚ የሆነው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ የተለያዩ የመንገድ፣ የድልድይ ግንባታዎችን ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ አቶ ዛይድ ከተነሱ በኋላ ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ጊዜ ቦታቸው ላይ ሰው አልተሾመም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አቶ ዛይድ አስተያየት እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2007 በጀት ዓመት ግንባታቸውን ለማስጀመር በዕቅድ ከያዛቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ ሰባቱን ከሳምንታት በፊት ለአገር ውስጥና ለውጭ ኮንትራክተሮች መስጠቱ ይታወሳል፡፡ ከእነዚህ ሰባት የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ አምስቱ ለውጭ ተቋራጮች ሲሰጡ፣ አራቱን የቻይና ኩባንያዎች መውሰዳቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ምንጭ:- ሪፖርተር
“ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል

November 4, 2014 05:51 pm By Editor Leave a Comment
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር “ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
“ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ” እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
“ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል” ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡
በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡ (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)
lørdag 1. november 2014
የተመስገን መታሠር እንዳሳሰባት ዩናይትድ ስቴትስ አስታወቀች የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በነበረው በተመስገን ደሣለኝ ላይ የተላለፈው የእሥራት ፍርድ እንደሚያሳስበው የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አስታወቀ፡፡
የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በነበረው በተመስገን ደሣለኝ ላይ የተላለፈው የእሥራት ፍርድ እንደሚያሳስበው የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አስታወቀ፡፡
ሃሳብን የመግለፅ መብታቸውን በመጠቀማቸው ታሥረዋል ያላቸውን ጋዜጠኞችም የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲፈታ ዩናይትድ ስቴትስ በድጋሚ ጥሪ እንደምታስተላልፍ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ አስታውቋል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ ወይም ሌላ ማንም መንግሥት ስላለ ሳይሆን ኢትዮጵያ መብቶችና ነፃነቶች የተከበሩባት ሃገር ነች፤
ሲሉ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል፡፡
ለተጨማሪና ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
በክበር ሲጠበቁ የነበሩት የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ባለስላጣን ለዳግም ህክምና ሳውዲ አረቢያ ሾልከው ገቡ ።
በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ስሞን ህመሙ ጠንቶባቸው ከሁለት ወር በፊት በሼክ አላሙዲን የግል አውሮፕልና
ተጭነው በድበቅ ለህክመና ሳውዲ አረቢያ መግባታቸው ይታወሳል። በወቅቱ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ የሚገኝ አንድ «ቡግሻን»
hospital እየተባለ የሚጠራ ሪፈራል ሆስፒታል የልብ ቧንቧ ማስፋት ህክምና ቢደረግላቸውም የባለስልጣኑ የጤነነት
ሁኔታ የሚጠበቀውን ያህል ለወጥ ባለማሳየቱ ለዳገም ህክምና ቀጠሮ ተሰቷቸው ከሳምታት ቆይታ በሃላ ወደ ሀገር ቤት
መመለሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል ።
bereketይህ በዚህ እንዳለ ዛሬም የአቶ በረከት ጤንነት መልካም ሁኔታ ላይ እንዳልሆነ ምንጮች የሆስፒታሉን የምርመራ ውጤት አብነት ጠቅሰው ይናገራሉ ። አቶ በረከት በጤነታቸው መታወክ ፍጹም መረጋጋት እንደማይታይባቸው የሚገልጹት እንዚህ ውስጥ አዋቂዎች ቀደም ሲል ባለስልጣኑ ህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት ወደ ሳውዲ አረቢያ በሚስጠር ለህክምና መግባታቸውን ተከትሎ በተለያዩ ድህረገጾች ዜናው በስፍት መናፈሱ በውስጣቸው በተፈጠረው አለመረጋጋት በልባቸው ምት አለመስተካከል በወቅቱ በቂ ህክማና መውሰድ እናዳልቻሉ ታውቋል። የአቶ በረከት የጤነንት ሁኒታ ዛሬም አስተማማኝ እንዳልሆነ የሚያውሱ እንዚህ የአይን እማኞች ከእለት ተዕለት የባለስልጣኑ የአካል መጠን በማይጠበቅ ሁኔታ መቀነስ እና የፊታቸው ገጽታ መለዋወጥ በውስጣቸው መልካም ነገር እንደማይታይ ያሳብቃል ብለዋል።
የአቶ በረከት ስሞኦን ህይወት ለመታደግ የአቅማቸውን ያህል ጠረት እያደረጉ የሚገኙ «ቡግሻን» hospital የሳውዲ አረቢያ ሆስፒታል ዶክተሮች ሰለበሽታው አደገኝነት ግንዘቤ በማስጨበጥ አቶ በረከት ከተለያዩ መጠጦች እና አይምሮ አደዛዥ እጾች መራቅ እንዳለባቸው እና የጤነንታቸው ሁኔታ አስተማማኝ ሁኔታ ከሲደርስ እረፍት መስውሰድ እንደሚገባቸው ሙያዊ ምክሮቻቸውን ለገሰዋቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከት ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲያቀኑ የህክምና ውጪያቸውን እየሸፈኑ ከሚገኙት ሼክ አላሙዲን ባሻገር ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት ሚስጠር መሆኑ አያሌ ወገኖችን በስፋት እያነጋገር ነው ። ከሁለት ወር በፊት አቶ በረከት እኩለ ለሊት ከቦሌ አይሮፕላን ማረፊያ ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕልና በድብቅ ለህክማን መግባታቸው ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወሬው የደረሰው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዘ-ሃበሻ እና ጎልጉል ድህረገጾች በተለቅቁ መረጃዎች መሆኑን የሚናገሩ ምንጩች ለሁለተኛ ግዜ ዳግም ህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲመለሱ በሼክ አልሙዲን በኩል በክበር «በፕሮቶኮል» ሊገቡ እንደሚቸል በወቅቱ ከጅዳ ቆንሳል ጽ/ቤት የወጡ መርጃዎች ቢያረጋግጡም የአቶ በረከት ስሞኦን እንደ ተለመደ በድብቅ ወደ ሳውዲ አረቢያ መግባት ባለስለስልጣኑ በውስጥም በውጨም ጥሩ ወዳጅ እንደሌላቸው የሚነገረውን ሃቅ ያጠናክረዋል ብለዋል ።
አቶ በረከት ትላንት በተደረገላቸው ምርመራ
የቅርብ ክትትል እንደሚያሻቸው የሚገልጹ የሆስፒታል መረጃዎች ባለስልጣኑ የተሰጣቸውን ምክር እና የተለያዩ መደሃኒቶቻቸውን ይዘው ከሆስፒታሉ ውጭ ወደ ሚገኘው ምስጢራዊ ማረፊያቸው ማቃናታቸው ተገልጾል፡ ይህ በዚህ እንዳለ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና መስረት አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ ማምሻውን ለአስቸኳይ ጉዳይ ህክምናቸውን አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመልሱ ምስጢራዊ መረጃዎቻችን አክለው አረጋግጠዋል ።

bereketይህ በዚህ እንዳለ ዛሬም የአቶ በረከት ጤንነት መልካም ሁኔታ ላይ እንዳልሆነ ምንጮች የሆስፒታሉን የምርመራ ውጤት አብነት ጠቅሰው ይናገራሉ ። አቶ በረከት በጤነታቸው መታወክ ፍጹም መረጋጋት እንደማይታይባቸው የሚገልጹት እንዚህ ውስጥ አዋቂዎች ቀደም ሲል ባለስልጣኑ ህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት ወደ ሳውዲ አረቢያ በሚስጠር ለህክምና መግባታቸውን ተከትሎ በተለያዩ ድህረገጾች ዜናው በስፍት መናፈሱ በውስጣቸው በተፈጠረው አለመረጋጋት በልባቸው ምት አለመስተካከል በወቅቱ በቂ ህክማና መውሰድ እናዳልቻሉ ታውቋል። የአቶ በረከት የጤነንት ሁኒታ ዛሬም አስተማማኝ እንዳልሆነ የሚያውሱ እንዚህ የአይን እማኞች ከእለት ተዕለት የባለስልጣኑ የአካል መጠን በማይጠበቅ ሁኔታ መቀነስ እና የፊታቸው ገጽታ መለዋወጥ በውስጣቸው መልካም ነገር እንደማይታይ ያሳብቃል ብለዋል።
የአቶ በረከት ስሞኦን ህይወት ለመታደግ የአቅማቸውን ያህል ጠረት እያደረጉ የሚገኙ «ቡግሻን» hospital የሳውዲ አረቢያ ሆስፒታል ዶክተሮች ሰለበሽታው አደገኝነት ግንዘቤ በማስጨበጥ አቶ በረከት ከተለያዩ መጠጦች እና አይምሮ አደዛዥ እጾች መራቅ እንዳለባቸው እና የጤነንታቸው ሁኔታ አስተማማኝ ሁኔታ ከሲደርስ እረፍት መስውሰድ እንደሚገባቸው ሙያዊ ምክሮቻቸውን ለገሰዋቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከት ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲያቀኑ የህክምና ውጪያቸውን እየሸፈኑ ከሚገኙት ሼክ አላሙዲን ባሻገር ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት ሚስጠር መሆኑ አያሌ ወገኖችን በስፋት እያነጋገር ነው ። ከሁለት ወር በፊት አቶ በረከት እኩለ ለሊት ከቦሌ አይሮፕላን ማረፊያ ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕልና በድብቅ ለህክማን መግባታቸው ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወሬው የደረሰው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዘ-ሃበሻ እና ጎልጉል ድህረገጾች በተለቅቁ መረጃዎች መሆኑን የሚናገሩ ምንጩች ለሁለተኛ ግዜ ዳግም ህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲመለሱ በሼክ አልሙዲን በኩል በክበር «በፕሮቶኮል» ሊገቡ እንደሚቸል በወቅቱ ከጅዳ ቆንሳል ጽ/ቤት የወጡ መርጃዎች ቢያረጋግጡም የአቶ በረከት ስሞኦን እንደ ተለመደ በድብቅ ወደ ሳውዲ አረቢያ መግባት ባለስለስልጣኑ በውስጥም በውጨም ጥሩ ወዳጅ እንደሌላቸው የሚነገረውን ሃቅ ያጠናክረዋል ብለዋል ።
አቶ በረከት ትላንት በተደረገላቸው ምርመራ
የቅርብ ክትትል እንደሚያሻቸው የሚገልጹ የሆስፒታል መረጃዎች ባለስልጣኑ የተሰጣቸውን ምክር እና የተለያዩ መደሃኒቶቻቸውን ይዘው ከሆስፒታሉ ውጭ ወደ ሚገኘው ምስጢራዊ ማረፊያቸው ማቃናታቸው ተገልጾል፡ ይህ በዚህ እንዳለ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና መስረት አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ ማምሻውን ለአስቸኳይ ጉዳይ ህክምናቸውን አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመልሱ ምስጢራዊ መረጃዎቻችን አክለው አረጋግጠዋል ።
Abonner på:
Innlegg (Atom)