የዩጋንዳ «ናሽናል ሬዚዝተንስ ሙቭመንት» ፓርቲ ፕሬዚደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒን እአአ ለ2016 ዓም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በዕጩነት ለማቅረብ የያዘው ዕቅድ ብርቱ ክርክር አስነስቷል።

ዮዌሪ ሙሴቬኒ እአአ ከ1986 ዓም ወዲህ በዩጋንዳ የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን እንደያዙ ይገኛሉ። ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ የሀገሪቱን ሕገ መንግሥት በተደጋጋሚ ባማሻሻል ካለፉት 28 ዓመታት ወዲህ ሀገሪቱን መምራታቸውን ቀጥለዋል።
በአንድ ወቅት የአንድ አፍሪቃዊ ሀገር ርዕሰ ብሔር ከአስር ዓመት በላይ በሥልጣን መቆየት የለበትም ሲሉ የተናገሩት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከሥልጣናቸው ለመውረድ ሀሳብ እንደሌላቸው የፖለቲካ ተንታኞች ገልጸዋል። በዩጋንዳ የሚታዩት ሁኔታዎች እንደጠቆሙት፣ በምሕፃሩ «ኤን አርኤም» በመባል የሚታወቀው ገዢው የዩጋንዳ «ናሽናል ሬዚዝተንስ ሙቭመንት» ፓርቲ እአአ በ2016 ዓም በሀገሪቱ ለሚካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ብቸኛው ዕጩ አድርጎ ለማቅረብ እየጣረ ነው። ሙሴቬኒ ለአምስተኛ የሥልጣን ዘመን በዕጩነት እንዲወዳደሩ የተያዘውን ጥረት የተቃወሙ ሶስት የመብት ተሟጋቾች ይህንኑ ተቃውሟቸውን ለምሥራቅ አፍሪቃ የፍትሕ ፍርድ ቤት አቅርበዋል።
rechts<br />
“>
“>
የፖለቲካ ታዛቢዎች እንደታዘቡት በገዢው ፓርቲ ውስጥ የሥልጣን ፉክክሩ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው። ይሁንና፣ እንደ ፖለቲካ ተንታኙ አንጀሎ ኢዛማ ግምት፣ ይኸው ፉክክር ለቀጣዩ ምርጫ ያን ያህል ስጋት የሚፈጥርባቸው አይሆንም።
« ፕሬዚደንቱ ቀጣዩን ምርጫ በተመለከተ እየተከተሉት ያለውን አሰራር ስንመለከት፣ ፉክክሩ ቀላል አለመሆኑን ለመረዳት እንችላለን። በተለያየ ደረጃ፣ ማለትም ከቀድሞ ታጋይ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ዴሞክራሲን ማጠናከር ከሚፈልገው የወጣቱ ትውልድም ፉክክር ገጥሟቸዋል። በቀጣዩ ምርጫ ግን ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ ከገዛ ራሳቸው የ«ኤን አርኤም» ፓርቲም ሆነ በጠቅላላ ከዩጋንዳ የፖለቲካ መድረክ ጠንካራ ተፎካካሪ ሊሆንባቸው የሚችል አንድም ተቀናቃኝ የላቸውም። »
አርያም ተክሌ
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar